ልጥፎች

ከኦክቶበር 13, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

መቼ ነው የህወሃት መኳንነት ሃፍረት የሚባል የሚሰራላቸው?

ምስል
አለማፈረን ግባ በሉት ¡ „አህዛብ ለምን ያጉረመርማሉ?“ መዝሙር ፩ ቁጥር ፪ ከሥርጉተ ሥላሴ 13.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። የእንጀራ ልጆች ፍዳ! ጫጫታ በረከተ በማህበረ ተጋሩ ሠፈር። መቼም እኔ ከወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌሰቶ ጋር ተብጥብጦ የተጋቱ አለማፈር ብቻ መሆኑን እዬተረዳሁኝ ነው። እንዲያውም አያፍሩም አሁን አዬር መንገድ ላይ ባለው ገመና። የተጠናከረ የሎቢ ተግባር እንዳይካሄድ እኮ መቼም ኢትዮጵያ የሚል አንድ ተቋም ብቻ እሱ ስላለ ነው እንጂ የመብት ረገጣው እኮ የኦሽትዝ ግፍ ያዬለበት ነው። ሰብዕዊ መብት ይከበር የሚሉ አገሮች እኮ የ አዬር መንገዱን አሰራር እንደጸዬፉት ማድረግ ይቻላል። ግን ከ አዬሩ ላይ ያለው ንጹህ ብሄራዊ ሰንድቅ አላማ ቃልኪዳን ስለሚይዝ ነው ዝም የሚባለው።   አሁን እዛ ያሉ የተጋሩ ሃላፊዎች ሳር ቅጠሉ እሱ በእሱ ሲሆን ትንሽ ብጣቂ ነገር እንዴት ልብ አይሰራላቸውም? አያፈሩበትም፤ በር ስትከፍትም፤ ኮሪደርም፤ መጸዳጃ ቤትም፤ ካፍተሪያም፤ ሜዳውም ላይ ሁሉም ቤተ ተጋሩ ሲሆን አይቀፍም! ህሊና ያለው ጥፍር ላይ ነውን?  በሩ ራሱ እኮ ጠረኑ እነሱን እነሱን ነው የሚለው። ወለሉም እንዲሁ ነው። በእነሱ ዘመን እኮ ነው ሰው እያዬ እዬሰማ እግሩ የተቆረጠው ምክንያት ተፈልጎ። በእነሱ ዘመን ነው ወንድ ልጅ የተንኮላሸው፤ በእነሱ ዘመን ነው ዘራፋ እንዲህ ባህል የሆነው፤ ምን ያልታዬ መከራ አለና። ቃለ ምልልሱ ሲታይ ጠያቂውም ተጠያቂውም ዘገባ አቅራቢውም ዘገባውን አስተላላፊውም ያው ነው ቤተ ተጋሩ። እዛ አዬር መንገድ አንድ ነገር ሲፈጠር አንድ ሰው ለዬት ያለ ለማግኘት ይችግራል። በውነት ይቸግራል። በጣም ጸያፍ ነገር ነው። ዋ! ነው የሰማይ ጦሮ የታዘዘ ዕለት። አሁን

በለው! የአቦ ሌንጮ ለታ ፈረስትነት።

ምስል
የአቶ ሌንጮ ለታ የኦሮሞ ፈርስት ፈገግታ። „አቤቱ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ፤ በእኔ ላይ የሚቆሙት ብዙ ናቸው።“ መዝሙር ፫ ምዕራፍ ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 13.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ቢስ አይይብን ዶር ለማ መገርሳ እና ዶር አብይ አህመድን ብለናል። የአፍ ሳይሆን የውስጥ ወልምታ እንዳይኖርባቸው አብዝተን እንጸልያለን። ውዶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ ወይ። ባለፈው አንዲት ሴት በተፈጥሯዋ አንድ ጡት አብቅላ በህልሜ አዬሁኝ ብያችሁ ነበር አይደል? እህቴ ስተፈታልኝ ኢትዮጵያ መከራዋን ተሻግራ አንድ የምትሆንበት ዘመን ይመጣል አለችኝ። እኔም እንደ አፍሽ ያድርግልን አልኩኝ። ዛሬ ስለተፈሪው ማንነት ስለ ኢትዮጵያዊነት ትንሽ ማለት ፈለግሁኝ። አንድ የጠራ ነገረ ማወቅ ፈለግሁኝ። ፍራንከፈርት ከዶር አብይ አህመድ ጋር ሥብሰባ እንዳለ አዳምጫለሁኝ። ወደ ፍሬ ነገሩ ከመሄዴ በፊት ስለፍራንክፈረት የነፃነት ትግል ዓውራነት፤ ለዴሞክራሲያዊ ተጋድሎ አዕምድነት ትንሽ ማለትን እሻለሁኝ። እንግዲህ ፍራንከፈረት የፖለቲካ ጭንቅላት አባ ወራዎቹ ያሉበት ቦታ ነው። አባወራ ነው ያልኩኝ እማ ወራ ሴት ፖለቲከኞች በአላዛሯ ኢትዮጵያ ስለማይታሰብ ነው፤ አብሶ ውጪ አገር ያው መፈናፈኛ የለም። ይቀኑብናል ወንዶቹ። ለምን? ልባቸው ያውቀዋል።  ወደ ቀደመው ጉዳዬ ልሳን ስመለስ ፍራንክፈርት ውስጥ በግራሞት እስኪ ይሁኑበት ብለው፤ በተደሞ የባጁ ስንት የሚያውቁ፤ ስንት ለኢትዮጵያ የደከሙ ወገኖች ከቅንጅት ግርግር ጋራ በተያዬዘ አንገታቸውን ደፍተው የተቀመጡ እንዳሉ አውቃለሁኝ። ዛሬ አሜሬካን ዲሲ ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አናት ሳይባል እንቅልፍ ላይ እነሱ በነበሩበት ጊዜ አውሮፓ በ90ዎቹ መጨረሻ በሳል የሆኑ፤ ሞጋች የሆኑ