ልጥፎች

ከጃንዩወሪ 14, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ጊዜውን ያላባከነ ሰው ሞተ አይባልም። አረፈ ይገልጽልኛል።

ምስል
      በሌላ በኩል ትውልድ የተካም ሞተ ሊባል አይገባም። ተክቷል እና። ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ሠርቷል። ጊዜው አልባከነም። እወላጅ አባቱንም፤ ባለቤቱንም በወል አጥቶ ያን ተቋቁሞ አገልግሎቱ ሳይቋረጥ ቀጥሏል። ጋዜጠኛው ፀጋውንም አልተላለፈም። ፀጋው ጋር ተዋህዶ ፀጋውን አስከብሮ በትውልዱ ድልድይ ሠርቶ፤ ባትሎ፤፥ተግቶ፤ ታትሮ ወደ ጠራበት ጽረ አርያም ሁሉንም ሰጥቶ ሳይሰስት፤ ሁሉንም ለግሶ ሳይንቆጣቆጥ እና ሳይለግም ወደ ዘላለማዊ ህይወቱ ገስግሷል። እያንዳንዱ ልጅ ሲወለድ መልዕክት፤ መክሊት፤ ጥሪ ይዞ ይወለዳል የምለው ፍልስፍና አለኝ።   እንዲሁም ትልቅ ሰው ሞተ አይባልም። ትልቅ ወንዝም ደረቀ አይባልም። ዕድሜ ዘመኑን ጥቅም ላይ የዋለ ቋሚ አሻራን በእጁ ያበጀ ትልቅ ሰው ህልው ነው። መንፈሱ ይኖራልና። ተግባሩ ይሰጣልና። ድርጊቱ ቁሞ ያስተምራልና። ዛሬ ጋሼ አማኑኤልን፤ ጋሼ ዘውዱን ጋሼ ተክሌ መጡብኝ። ድምፃቸው ሽው ውል አለብኝ። ሦስቱም የጀርመን ድምጽ የአማርኛ ቋንቋ ክፍል ባልደረቦች ኃላፊወች እና አስተዳዳሪወች ነበሩ። ለዛቸው ቃናቸው ጣማቸው ትውልድን በሙያ የመቅረጽ ቅንነታቸው ልዩ ነበር።   ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻም መልዕክቱን አድርሶ፤ ጥሪውን አንሰራፍቶ፤ መክሊቱን አቆላምጦ እና አለምልሞ የኖረ ሰው ነበር። ፍቅር ሰጥቶ ፍቅርን በገፍ ያለ ገደብ ያገኜም ዕድለኛም ሰው። ሚሊዮኖች የዚህ ዕድል ባለቤት ሳይሆኑ ያልፋሉ። እሱ ግን ዕድለኛ ነው። ሁሉን አይቶ፤ ሁሉንም አጣጥሞ ተወዶ፤ መውደድን አከፋፍሎ የኢትዮጵያን ህዝብ ታላቅነት በውል እንዲታይ ምክንያት ሆኖ አርፏል። እኛም ተከተይ ነን። ቀሪ የለም። ልጁን ጃፒ እና መላ የኢትዮጵያን ህዝብ ቤተሰቡን እግዚአብሄር ያጽና። ቢያንስ ለቀሩት ጋዜጠኞች ፍቅርን ክብርን እንለግስ። ጨምተን ታግሰን ጋዜጠኞችን እንውደድ። እ

"የአማራ ፋኖ ትጥቅ እንዲፈታ ፌድራሉ ወሰነ" #ፋኖነት ደሜ ነው መለያዬ!

ምስል
  "የአማራ ፋኖ ትጥቅ እንዲፈታ ፌድራሉ ወሰነ" ይላል ፋሲሎ ኤችዲ። #ፋኖነት ደሜ ነው መለያዬ!     ያሰጋኛል ይላል ዝልግልጉ የኦህዴድ ሥርዓት የአማራን ፋኖ። ይህ ለአማራ ህዝብ ብቻ ነው። ይህ ማለት የአማራ ህዝብ አትኑር ማለት ነው። ምክንያቱም እያንዳንዱ የአማራ ህዝብ ፋኖ ነውና። ይህ ማለት እያንዳንዱ የአማራ ልጅ ሲወለድ ፋኖ ሆኖ ነው የሚወለደው። አያውቁም። ጎንደር ልጅ ሲወለድ ቅቤ ይውጣል። ቅቤውን በአፈሙዝ እንዲውጥ ይደረጋል። እኔ እራሴ አቀባብዬ መተኮስ እችላለሁ። ሰልጥኛለሁ። ብሄድ ቀጥታ ውጊያ ወረዳ መግባት እችላለሁ። የከተማ ልጅ ነኝ። ግን ትውፊታችን ያ ነው። ኮልቷ፣ ክላሽኗን ተንተርሼ ነበር እማድረው። አዋና። ጫካዋንም አውቃታለሁ። ጉድቧንም። አቀበት ቁልቁለቱንም። ቆላ ደጋውንም። አትሰቡት። መላ ህዝቡ ይሸፍታል። ይሸፍትም! ያን ዘልዛላ የግርባው ብአዴን የምድር እንቧያችሁን ይዛችሁ ትቀራላችሁ። የምርኮ አለቃችሁን ጅጅጋ መላካችሁን ሰምቻለሁ። ለምን እንደሆን አውቃለሁ። አቶ ሙስጠፌ ኡመር። ተራቸውን የሚጠብቁ ለእርድ የተዘጋጁ ቀጣይ ኢላማችሁ ናቸው። አማራ ክልል አንድ ነገር ስታስቡ ለሚዛን እምትሮጡት ጅጅጋ ነው። አይምሰላችሁ። ሲከር ይበጠሳል። ሲሞላም ይፈሳል። አይደለም እናንተ ዲሞክራቶች በቀጣዩ ምርጫ የሚገጥማቸውን ፈተና ያወቁት አልመሰላቸውም። የአማራ ህዝብ አቅሙ ያልናቃት፣ ያልሸፈተባት፣ ያልተዋት ኢትዮጵያ ናት። የትናንትም፣ የዛሬም፣ የወደፊትም የአቅማችን ፏፏቴ ከዛ ይመነጫል። ትንታጎችን ሚሊዮኖችን በዚህች ቅፅበት ታጣላችሁ። ድምፃቸውን አጥፍተው በዝምታ ውስጥ ያለ አሉና። ምነው የእናንተ ኦነግ በጠራራ ጠኃይ ሥልጠና ሲወስድ፣ ሎጅስቲክስ ስታሟሉ አልጨነቃችሁ? ነፍሳችሁን ላቆዬ የአማራ ፋኖ ብድሩ ይህ ነውን? አትሰቡት። ሽፍትነ

12.01.2020 ከቶ አሁንስ ተረኝነት አለመሆኑን ተረዳን ይሆን?

  ከቶ አሁንስ ተረኝነት አለመሆኑን ተረዳን ይሆን?   ይህ መከራ ማለዳነቱ ለኢትዮጵያ ነው። አፍሪካም ቀጣይ ናት። የፖለቲካ አስተሳሰቡ ከፍ ወደ አለ ደረጃ ማደግ አለበት የምለው ለዚህም ነው። የሶልዳሪቲ ትግልም ያስፈልጋል የምለውም ለዚህ ነው። ጉዳዩ የተረኝነትም፣ የፈረቃም አይደለም። ከዛ ከፍ ያለ ነው። የኦሮሚያ አገራዊነት ዕወጃ ነው። የአማራ ሊሂቃን የተጨፈጨፋበት ሚስጢርም ይኽው ነው። የሰኔ 15 ቀን 2011 ዓም ትልም ይኽው ነበር እገታ። አዲስ አበባን ለኦሮምያ ርክክቡ የተፈፀመው መስከረም 5 ቀን 2011ዓም ነው። ኢትዮጵያም እንዲሁ። ዕውነቱ ይህ ነው። ስለዚህ በስክነት ቀጣዩን መራራ ተጋድሎ አህዱ ለማለት የጥምኖ ጊዜ መውሰድ እና በጥበብ ቀጣዩን ምዕራፍ መጀመር ነው። መደናገጥ አያስፈልግም። የሰው ልጅ ደህና ከሆነ ፈቃደ እግዚአብሄር በራሱ ጊዜ የሚሠራው ታምር ይኖራል። ይህም ለበጎ ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ ይገባል። ከዚህ ቀጥሎ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን በቁም እስር ላይ እንደነበር ይታወቃል። በቀጣይ ምን ሊያደርጉት እንደሚችሉ አይታወቅም። መራራው ጊዜ የገባቸው ጥቂት ስለነበሩ አሁንም አዲስ የመማሪያ ሌሰን ለተኙ ሁሉ ተሸልሟል። ጃዋሪዝም ይህን ይመስላል። የፈለገውን የማስፈፀም ሙሉ አቅም አለው። ኢትዮጵያዊው ሰው ቀፎውን ነው ያለው። ተቦርቡሮ፣ ተጎርጉሮ ደመ ነፍሱን ነው የሚንቀሳቀሰው። ነገስ? በእንቅልፋችን ልክ ይወሰናል? አይዞን። ያ እንዳለፈው ሁሉ ይህም ያልፋል። ፅናት ብቻ ሳይሆን በአብይዝም እና በተደማሪ የወግ ገበታ እራስን አለመገበር ይጠይቃል። የባልደራሱ ባለ አደራው ትውልዳዊ ድርሻውን በሚገባ ተወጥቷል። አደራውን በሚገባ አሳክቷል። ቀጣዩ ጉዳይ ህልውናውን የተነጠቀው ህዝብ የልዕልና ልቅና ምላሽ ነው የሚጠበቀው። ኢትዮጵያ አጥር ውስጥ ናት የ

በትውልድ ግንባታ ላይ መብት ኖረንም አልኖረንም መሳተፋችን አይቀሬ ነው።

ምስል
  በትውልድ ግንባታ ላይ መብት ኖረንም አልኖረንም መሳተፋችን አይቀሬ ነው። "ዬሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱)     አጤ ፌስቡክ ከቶ ደስብሎህ ሰነበተን? ግብት ስል ማስጠንቀቂያውን ይዘህ ከቸች ትላለህ። ዬሆነ ሆኖ ዛሬን ዕለቱን በጦቤያው ጥር 6/2015ን ቅኝት ላድርግ ብዬ ጎራ ብያለሁኝ። ዋርካ ያለው ጥላ ይኖረዋል። ዬተከበረው ዬሁለመና ሁለመና ጋሽ ግርማ በዬነ፤ ዬተከበረው ዬሁለመና ሁለመና ጋሽ ይልማ ገብረአብ መኖራችሁ ተስፋችን ነው። የተስፋ እርግብ በር። ለዝግጅቱ ግርማ ሞገሱ ጉልላቱ ነበራችሁ። ኑሩልን። አሜን። ዛሬ ዬፋና ላምሮት ዬአሸናፊወች አሸናፊ ውድድር ነበር። ስከታተለው ነበር። አስተያዬትም ስሰጥበት ነበር። ትውልድን ለመቅረጽ ዬሚደረገውን ሁለገብ ጥረት መደገፍ የዜግነት መብት ሳይሆን ግዴታም ነው። ዬእኔ እንደ ጥሪዬ ዬማዬው ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ ላይ ይህ መጀመሩ አበረታች ነው። ሙዚቃ ዬመኖር የውስጥ ሙዳይ ነው። ደስታህን፤ መከፋትህን፤ ሲቃህን ቅኔህን፤ ቃናህንም፤ ታሪክህ፤ ማንነትህ፤ ነፃነትህ የሰጠህ የምትገልጽበትም። ሙዚቃ ላይ እኔ እምብዛም ብሆንም ግን በጥበብ ቤተኝነቱ፤ በሥነ - ፁሁፍ ለዛ እና ጣዕሙ መመሰጤ አይቀሬ ነው። ዬፋና ላምሮት ዬሥራ አስፈፃሚው ኃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው "ዬእኔ፤ ያገባኛል" ዬሚል ስሜት ፋና ላምሮት ፈጥሯል ሲሉ መግቢያቸው ላይ ገለፁ። አወን ተፈቀደልንም፤ አልተፈቀደልንም እንሳተፋለን። እኔ እርግብ በር፤ ዬተስፋ በር ሁለት መጽሐፌን የፃፍኩት፤ የምክር ዬመነሻ ሃሳቦች ናቸው ዓለም ዓቀፍ ውድድሮችን እዬተመለከትኩ ነበር። ክፍተቶችን አይቼ ገምግሜ ትውልድ እንዴት ይቀረጽ? ትውልድ እንዲቀጥል እንዲህ ያሉ ነፍስ ሆነው ነፍስ ዬሚዘሩ

Das Reinste in der Liebe ist Klarheit.

ምስል
  Das Reinste in der Liebe ist Klarheit.    Das Wasser, das vom Himmel kommt, ist sauber. Liebe braucht Klarheit, wie Wasser am Himmel. Dies ist normalerweise nicht der Fall. Dies ist eine Lektion, die wir aus der Natur der Liebe gelernt haben. Transparenz ist übrigens ein eigenständiges Thema. Deshalb sage ich, die Natur der Liebe ist der Ozean. Die Natur der Liebe selbst kann dir inneren Frieden bringen, wenn du daran denkst. Die Natur der Liebe ist eine facettenreiche Generation. Für mich ist die Natur der Liebe eine Generation. Oder der 13. Planet. Was wir noch nicht recherchiert haben. Abgesehen von der Natur der Liebe, wie viele moderne Projekte hat unser Planet geplant? Können wir die Jahre seit der Erschaffung der Welt zählen? Kann er es platzieren? Bitte gehen Sie vor Gericht und fragen Sie die Wissenschaftler? Auf Wiedersehen, bis wir uns in meinem nächsten Beitrag treffen. Ich wünsche Ihnen einen schönen Tag. Gott das Heilige Land Schweiz; Heiliges Land Äthiopien; Schütze di

አርበኛ ጎቤ የዘመን ንጥር

ምስል
  አርበኛ ጎቤ የዘመን ንጥር   ጥቃት አውጬ ጥንድ የብረት አጥር። የዕውነት ዓይን ባለ ሙሉ ዝናር የእሱዪ አባት የዘመን በር አንበሳው ጎቤ፣ አርበኛው ጎቤ አታስደፍር! ዋዋ ዓለሙ ለምለሙ፣ ሲሳይ አዳሩ ለአድባሩ፣ ሁሉን የሰጠህ ለቃሉ፣ ለውለ - ግብሩ የኪዳን ማደሪያ ነው ሥሩ! የፍኖ አባት ግንደ ፍኖተ - ዘሩ አትንኩኝ ባይ፣ ሲነካበት አድባሩ! የአማራ ትርታ ህብርህ! ያበራል ገና ጉልላትህ። ይደምቃል ዘውዱ በበላይህ ዘልቋል ዘምኗል ፋናህ! ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 14/01/2022 18.59 ሲዊዘርላንድ ቪንተርቱር

የገዳ የሰበር የሲቃ - ህቅታ - በትንታ - ህማማት!

ምስል
  የገዳ የሰበር የሲቃ - ህቅታ - በትንታ - ህማማት!   ስክን እርግት ህይወት! ዘመኑ በመጨመት ይሁን በአስተውሎት። ማረግረግ በጥድፈት አያሻትም እናት ብልህነት - በስክነት ለሱባኤው ህማማት! ሲተመተም ሲጉተመተም የህምምታ አውዳመት የሰኔል የቹቻ ረከቦት እሽቅድድድምሾ የአልቦሽ ሂደት። የቃጠሎ የአመድ ቅልቅሎሽ ግሳት የድንጋይ የአካፋ የዶማ ክሳት የአፈር ደለለል ሁካታ በእልልታ ያለለፈው የገዳ ሆታታ የለት ተለት // ቱማታ የሰበር ትንታ! ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 14/01/2022 18.31 ለዘመነ ኦህዴድ ይሁንልኝ።

#የአብን ዕርገት ወይንም ስርገት ቢያንስ አዲስ አበባ ላይ?

ምስል
  #የአብን ዕርገት ወይንም ስርገት ቢያንስ አዲስ አበባ ላይ?     #ይህን የመንግሥት ብቻ ሳይሆን አቤቶ አብንም ሼር ማድረግ ይኖርበታል ችግሩን። #አቤቶ የአዲስ አበባው ብአዴንም ከታጣፊ አልጋው ተነስቶ አንድ ሊለው ይገባል። እነ ዶር ሂሩት ካሳም። ሁሉም ተጠያቂ ነው። ////////-------------////////// # #ከአቶ ሳተናው በላይ ገፅ የተገኜ ዩአቶ አባይ ዘውዱ ዘገባ። "ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተፈናቅለው በአዲስ አበባ አስኮ መናኽሪያ የደረሱ ከ300 በላይ አማራዎች እርዳታ እየጠየቁ ነው። አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ ጥር 6 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ ሸዋ ከኦሮሚያ ክልል በአማራዊ ማንነታቸው ተለይተው ጥቃት የደረሰባቸው ወገኖች አዲስ አበባ አሰረኮ መናኽሪያ ይገኛሉ። የተፈናቀሉትም ከምስራቅ ወለጋ ዞን ስቡስሬ፣ ጎቡሰዮ እና ጉዳያ ቢላ እንዲሁም ከምዕራብ ሸዋ ዞን ባኮቲቤ ወረዳ መሆኑን ገልጸዋል። ከጥር 16 ቀን 2014 ጀምሮ ተፈናቅለው አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ እየለመኑ ዘመድ ያለው በየዘመዱ፣ በየቤተ ክርስቲያኑ፣ በየመስጊዲዱ እና በየበረንዳው እየተጠለሉ መቆየታቸውን ይገልጣሉ። አስኮ መናኽሪያ ውስጥ ነው ያለን ቁጥራችን ከ300 በላይ ይሆናል የሚሉት የአሚማ ምንጭ በማንነታቸው ምክንያት በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ እና በግብረ አበሮች መጠቃታቸውን አስረድተዋል። መንግስትም ሆነ የሰብአዊነት ጉዳይ ይገደናል የሚሉ ወገኖች ትኩረት ነፍገውናል የሚሉት ተጎጅዎቹ ብርዱ፣ጸሀዩ እና ርሃብ እየተፈራረቀብን ለከፋ ችግር ተዳርገናል ብለዋል። ድጋፍ የሚያሰባስቡ በጎፈቃደኞችም በከፍተኛ ስጋት ውስጥም ሆነው ከፖሊስ እየተሸሸጉ በጎ የሆነውን ነፍስ የማዳን ስራ እንደሚፈጽሙ ተናግረዋል። ተፈናቃዮች ጥር 5 ቀን 2014 የተወሰኑ የፖሊስ

ፀጋዬ ራዲዮ ላይፍ ላይ ነበር። ዛሬ ጥረ 14 ቀን 2021 የመጀመሪያ ሴንዱንግ ነበር ለአዲሱ ዘመን።

ምስል
  ጋዜጠኝነት ነፍስን የሚገራ ልዩ ሙያ ነው። ከዚህ ሙያ ውጪ መኖር ህልውናን ማጣት ሆኖ ይሰማኛል። ኖርኩኝ እምለው የፀጋዬ ራዲዮን ፕሮግራም ስሰራ ብቻ ነው። ወዘተረፈ ፈተና ልክ በማይወጣለት ትዕግስት እና ቅንነት ከአለ አንድ አይዞሽ ባይ 16 ዓመት ተቆጠረ። ስፖንሰር የለውም። አጋዥ የለውም። ፈታኞቹ ሊያዘጉት የሚታትሩት የራሳችን ወገኖች ግን ብዙ ናቸው። ያው እኔ ሳልፍ የፀጋዬ ሥም መነሳቱ ይቆማል። ግን እነ ችኩል ይጣደፋሉ ስጠራ ለሚከረቸመው ይዋጋሉ። ያልታደሉ።!!!    https://www.lora.ch/programm/alle-sendungen?list=Tsegaye   ፀጋዬ ራዲዮ ላይፍ ላይ ነበር። ዛሬ ጥረ 14 ቀን 2021 የመጀመሪያ ሴንዱንግ ነበር ለአዲሱ ዘመን። ራዲዮ ሎራ በሰባዕዊ መብት ጉዳይ የሚሠራ የኮሚቲ ራዲዮን ነው። ያው በወር እንደ አቅማችን ክፍያ እንከፍላለን። በኮሞሽን ነው የሚስተዳደረው። ኮሚሽኑ በአባለቱ የተመረጡ ናቸው። ደሞዛቸውን አባላቱ እና በጎ አድራጎት ድርጅቶች ይደጉሙታል። ማስታወቂያ አይሰራበትም። ክልክል ነው። ሰፋፊ የሰባዕዊ መብት ዝግጅቶችን፤ ኮንሰርቶችን ያዘጋጃል። የጸጋዬ ራዲዮ በብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ሥም የተመሠረተ ነው። ለእሱ መታሰቢያ ነው። ብዙ ፈተና አስተናግጄበታለሁኝ ዕጣ ነፍሴኢን። ያው በቅሎ መታዬት ጸሩ የሆነው ግንቦት 7 እስኪበቃው ታግሎታል። ግን እስካሁን አልቆመም። አለ። የእኔ አስትንፋስ እስካለች ድረስም ይቀጥላል። ሥሙ ግን የቅኔው ልዑል ብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን ተተክሏል። ይህ ነበር ተጋድሎው። ተሳክቶልኛል። እአከ2008 አስከ 2021 ድረስ ቀጥሏል።    ኢሳት ከመፈጠሩ በፊት የተፈጠረ ራዲዮን ነው። ብቻዬን ነው እምሠራው። አገር ማለት ምን ማለት ነው የሚል የልጆች ፕሮግራም ነበረው። እፍታ፤