ልጥፎች

ከኖቬምበር 19, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አችን ከትከት ብሎ ከልቡ ሳቀ - ሐሴቱን ስለጨበጠ። ተመስገን!

ምስል
አችን! „የጻድቃን መንገድ ግን አንደ ንጋት ብርሃን ነው። ሙሉ ቀንም እስኪሆን ድረስ እዬተጨመረ ይበራል“ መጽሐፈ ምሳሌ ፬ ቁጥር ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 19.11.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዝ ·       ጠ ብታ። አችን አማራበት። አችን ተሞሸረ። አችን ጫጉላ ላይ ነው። አችን  ጠሐይ ፍንትው ብሎ ወጣለት። አችን ከልቡ ከትከት ብሎ ሳቀ  ሐሴቱን ስለጨበጠ። አችን ደስታውን እያጣጣመ ነው። አችን  ለእሱም ዘመንም አዬው ወጣለት፤ ወፊቱም የምሥራች አዋጣችለት። ተመስገን!  ዘመን ጥሩ ነው። ዘመንም መስታውት ነው። ዘመንም ሂደት ነው። ዘመንም ዜና ነው። ዘመንም ታሪክ ነው። ዘመንም ህይወት ነው።  ዘመንም መኖር ነው። ዘመንም ገላጭ ነው። ዘመንም ተነባቢ ነው፤፡ ዘመንም አናባቢም ነው። ዘመንም ህግ ነው። ዘመንም አይቀሬ ነው። ዘመን ሰጥ አዎንታዊ ሲሆን ደግሞ ሽልማት ነው። ለዛውም ሰው ሰራሽ ያልሆነ። ·       መ ሆን። የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ የመሪዎች ጉባኤ በሰላም መጠናቀቁን እና አስከምልክቶ  ጠ/ሚር አብይ አህመድ የሰጡትን መግለጫ በልዩ ተመስጥዖ ነበር ያዳመጥኩት። እኛዊነት በግርማ ሞገስ ስላአጨጌ። ነፍሴን የማረከው እንዲህ የሚለው ነው „ አችን “  አገራዊ ሃላፊነት ለተወጡት በፍጹም ቅንነት ከልብ እና ከነፍሳቸው በማቀረብ ጠ/  ሚር አብይ አህመድ በራሳቸው ውስጥ አጥልቀው ከአንጀታቸው  ነበር እንዲህ ያሉት „ዲፕሎማቶቻ አችን፤ አሸከርካሪዎቻ አችን፤   የበራራ አስተናጋጆ አቻችን፤ ፓይሎቶቻ አችን፤ የአውሮፕላን ጣቢያ ሰራቶኞቻ አችን፤ ባለሆቴሎቻ አችን፤ የሆቴል ሠራተኞቻ አችን፤ የትራፊክ ፖሊሶቻ አችን፤ የጸጥታ አካላቶቻ አችን፤ የአዲስ አባባ ወጣቶች ተማሪዎችን እና  መላው

መምህር።

ምስል
መምህር። „እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።“ መጽሐፈ እዮብ ምዕራፍ ፴፬ ቁጥር ፲፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ  19.11.2018 ከጭምቷ ሲወዘርላንድ። „ተፈጥሮ አድሎ የሰጠንን ሀገር ተጠቅመን መቀየር ያልቻልነው እውቀትን የመፈለግ ዝንባሌያችን ሽርፍራፊ ፍራንክ ለመለቃቀም ከምናደርገው ጥረት በእጅጉ የተለያየ መሆኑ ነው፡፡ … ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ነች፡፡ ከማንም የተሻለ የማድረግ አቅም እኛ ውስጥ አለ፡፡ እኛ ያጣነው ዊዝደም ነው፡፡ ”  ከዶር አብይ አህመድ /አሜኑ/ የተወሰደ። ·        መቅደም ዕሳቤ። ሰሞኑን በመወሰድ ላይ ያለው እርምጃ መምህር ነው - ለእኔ። መምህርነቱ በሁለገብ ነው። መምህርነቱ ጸያፍነት መጸዬፍ እንዲቻል የሚያደርግ ነው። ከሁሉ በላይ ማንም ሰው ከህግ በላይ አለመሆኑን ማሳዬት መቻል ሌብነት፤ ስርቆት ዶክትሪኑ አድርጎት ለኖረው የወያኔ ሃርነት ትግራይ አውራ መንገድ ማክተሚያው የብሥራት መባቻው ነው። ትውልድ እንዲሞት የተፈለገበት ይህ መንገድ ትውልዱን ከታማኝነት ትውፊታዊ ማዕቀፉ ያወጣ መቅሰፍት ነበር ሌብነታዊ ጉዞው እና መካተቻው።  ይህን ጠ/ሚር አብይ አህመድ የሳይንስ እና የቴክኖሎጂ ሚኒስተር ሚንሰተር በነበሩበት ወቅት ከያንያንና እና ጋዜጠኞችን ባነጋገሩበት ወቅት እንዲህ ብለውት ነበር። እኔ የ ኢሳቱን የማማ እዘጋጅ ጋዜጠኛ አቶ ማስረሻ ዓለሙን የዛሬ ዓመት በሞገትኩበት ጊዜ ማጠቀላዬን ስሰራ በዚህ መልክ ነበር። ያን ጊዜ አሰሪው ድርጅትም ተው አላለውም ነበር። አልቆነጠጠውም ነበር። የሆነ ሆኖ  እንሆ ከዛ እንነሳ እና ወደ ዛሬው በኽረ ጉዳዬ እንገባለን። በጎ ህሊና እና ቅን ልቦና በዶር አብይ አህመድ ን