ኢትዮጵያዊው ዕውቅት የህልውና አደጋ ላይ ነው።
· ዕውቀትም ስደት ላይ ነው፤ እዬነደደ። · ልሙጧ ኢትዮጵያም ታጭታለች …. · ኢትዮጵያዊው ዕውቅት የህልውና አደጋ ላይ ነው። · ኢትዮጵያን የበጃት ጥበብ ቃጦሎ ታዞበት እየጋዬ ነው … ዕለተ ማክሰኞ ማዕዶተ ይግቡ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። „ዝም ብዬም የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።“ (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ 3 ቁጥር 17) · ኢ ትዮጵያዊው ዕወቀትም፤ ኢትዮጵያዊው ጥበብም ነዲድ ላይ ነው። · ኢትዮጵያ በጠላቷ እጅ ወድቃለች እና። o ዕ ውቀት የጀንበር ሥራ ነውን? ዕውቀት ህሊናዊ አቅም ነው በእኔ ዕድምታ። ፍልስፍናም፤ ጥበብም፤ ሳይንስም ነው። ያ ህሊናዊ አቅም በተለያዬ ሁነት ሊገኝ ይችላል። o ዕውቀት ዘርፈ ብዙም ስጦታ ነው። በአራት ከፍለን ልናዬው እንችላልን። (1) በ ትምህርት በሥልጠና የሚገኝ፤ ክህሎት እንደማለት … (2) በ ልምድ በሥልጠናም ከሥልጠና ውጪም የሚገኝ የተመክሮ ክፍል ነው። (3) ከፈ ጣሪ የሚገኝ የብልህነት ዘርፍ ነው። (4) የተለዬ ጸጋ ጥበብ የምንለው ነው፤ ያደላቸው በገኃዱ ዓለም ተምረው ተመረቅው፤ በተማሩበት የዕውቀት ዘርፍ ዕድል አግኝተው ሲሰሩበት የህልና ንድፉ ከተግባር ጋር ሲዋደድ፤ በተጨማሪም ፈጣሪ አምላክ ሳይማሩ ጥበብ እንደ ተሰጣቸውም በድርብነት ብልህነትም የጥበብ ጸጋው ሲኖራቸው እንኝህ ሙሉዑ የሆነ ሰብዕና ያላቸው ይሆናሉ። የፈጣሪ ስጦታ ምንም የቀለም ትምህርት ሳይገበዩ በተፈጥሯቸው ብልህ፤ አዋቂ ሆነው የሚፈጠሩ አሉ። ኢትዮጵያን ያበጃት