ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 18, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ወርሃ የካቲት ለእኔ የቅኔው ልዑል፤ #ፓን አፍሪካኒስቱ የብላቴው ጸጋዬ ገ/ መንፈስ የሚከብርበት ዓውዴ ነው። ለእኔ ጸጋዬዚም + ኢትዮጵያኒዝም + አፍሪካኒዝም= #የዕውቀት ዘርፍ ነው ብዬ አምናለሁኝ።

ምስል
  ወርሃ የካቲት ለእኔ የቅኔው ልዑል፤ #ፓን አፍሪካኒስቱ የብላቴው ጸጋዬ ገ/ መንፈስ የሚከብርበት ዓውዴ ነው። ለእኔ ጸጋዬዚም + ኢትዮጵያኒዝም + አፍሪካኒዝም= #የዕውቀት ዘርፍ ነው ብዬ አምናለሁኝ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።        #ምዕራፍ ፲፰    #እፍታ ።   ክብሮቼ ማዕረጎቼም ቤተ ሥርጉትሻ ቅኖች ሆይ! ዛሬ የ፲፰ ዓመት መንፈሰ ጸጋዬ ጉዞዬ በምዕራፍ ፲፰ቱ የአጤ ፌስቡክ ማዕዴ ዘለግ ብሎ ይቀመራል። እኔ ወደ ብላቴው አቀናሁ ወይንስ እሱ ወደ እኔ መጣ። ቅኔውን ለባለቅኔወች፤ ዕድምታውን ለዕድምታ ባለሙያ ሊቀ - ሊቃውንታት ልተወው።    ብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንን በሚመለከት ለሙሉ ፲፰ ዓመታት የተጋሁበት፤ የተከሰስኩበት፤ ብዙ ፈተና ያስተናገድኩበት፤ ብዙም የተንገላታሁበት፤ የተገለልኩበት፤ ባን በሉት ብሎክ በእኔ ላይ ፈርሰስ ብለው ወክ እንዲህ ያሉበት፤ የተንበሸበሹበትም በኽረ ጉዳዬ ነው። በፓልቶክ በሉት፤ በድህረ ገጽ፤ አሁን አዲስ ገብ በሆነው የሚዲያ ዕድል ዩቱብም ሳይቀር #ፋክክሩ ለወረት ይደራል፤ የዘለቀ ግን የለም። ለምን? #በድንግልና የተወጠነ ስለማይሆን። አንድን የዕውቀት ዘርፍ ሊያዘልቅ የሚችለው የውስጥ #ቅንነት እና ንጽህና ብቻ ነው።    የጸጋዬ ድህረ ገጽ ነበረኝ። በቦርድ ነበር የሚመራው። የልጆች ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ የነበረው ድህረ ገጽ ነበር። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተገዢነት፤ ተጠቅላይነትን ይሻ ስለነበር አሻም በማለቴ ቦርዱ ተበተነ። ግን ብቻዬን እኩል የጀመርኩት የጸጋዬ ራዲዮ ስለነበር። ያ ቀጠለ። የመጀመሪያው ፕሮግራም ሲደመጥ ነበር በአክራሪ ኦሮሞነት እና በአክራሪ ኦርቶዶክስነት የተከሰ...

#ነገረ #ራያ።

  #ነገረ #ራያ ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰   ወደ 60 ሺህ የሚጠጉ ራያወች በህወሃት ምክንያት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው እዬተንገላቱ ስለመሆኑ ቢቢሲ የአማርኛው ዘገባ መረጃውን ሰጥቷል። ለእነኝህ ተፈናቃዮች ሁነኛ #ባለቤት የተገኜ አይመስልም። እርዳታ የሚያደርግላቸውም አላገኙም። በውነቱ #ባለቤትም ያገኙ አይመስልም።    ሚኒስተር በለጠ ሞላ ምን ያስባሉ (ዶር)???? ሃይቅ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ የሚኒስተሩን ሥም አጉልተው ሲያነሱ የሚያስደስት ከሆነ ኃላፊነትን በቀጥታ በሚመለከት ጉዳይ ፋይዳ ያለው ተግባር ተፈጽሞ ቢሆን መልካም ነው። መግለጫ ለ60ሺህ ግፋዓን አፍ ማርጠቢያ ስለማይሆን። ለነገሩ ማህበራዊ መሠረት አልቦሽ የመሆን ሁነት ነው ያለው።    የአማራ ክልል በወዘተረፈ ችግር እየተጣደፈ ነው። የራሱን ችግር ማስተዳደር ያልቻለ ክልል፤ ተጨማሪ ብሄራዊ ግዴታ ሲታከልበት ለራሱ የውስጥ ችግር መብቃት ያቃተው ሌላ ሃላፊነት #የሚያስቃስት ነው የሚሆነው።    በዚህ 8 ዓመት በዕድሉ ጨምቶ እየተጠቀመ ያለው #ሱማሌ ክልል ነው። የወደፊቱ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሚዛንም ወደዚህ እንደሚያደላ አስባለሁኝ። ከታች ጀምሮ የአወቃቀሩ ስታይል ብቃት ባላቸው ወጣቶች የተገነባ ነው። ሰላምም ነው። በሲዳም የተበራከተ ስሞታ አልሰማም። ደቡብም እንዲሁ። የጠቅላይ ሚር #የአትኩሮት አቅጣጫም #ደቡብ - ገብ ነው።    የሆነ ሆኖ ነገረ ራያ ጉዳይ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረታቸውን #ቢያቀኑለት ስል በትህትና አሳስባለሁኝ። ለነገሩ በደባርቅ #ከሱዳን የተፈናቀሉ ወገኖች እንዳሉም ሪፖርተር ላይ በዚያ ሰሞን አንብቤያለሁኝ። ደብረብርሃ...