የፖለቲካ እስረኞች ወገኖቼ #አዋን ይፈቱልኝ፤ በእስር ቤት እያሉ ወገኖቼ ጤናቸው ይጠበቅልኝ እንጂ አይደለም በአክብሮት እና በትህትና #ተንበርክኬ ብለምን የሚቀርብኝ ቅርጥፍጣፊ ክብር የለም።
የፖለቲካ እስረኞች ወገኖቼ #አዋን ይፈቱልኝ፤ በእስር ቤት እያሉ ወገኖቼ ጤናቸው ይጠበቅልኝ እንጂ አይደለም በአክብሮት እና በትህትና #ተንበርክኬ ብለምን የሚቀርብኝ ቅርጥፍጣፊ ክብር የለም። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፯ እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ገና በጋሜ እና ታሬዬ ዘመን ጀምሮ ተከብሬ ነበር በፖለቲካ ተግባር ተኮትኩቼ ያደግኩት። እንደዛሬው ማህበራዊ ሚዲያ ቢኖር ከቶፕ ሁለገብ፤ ተከባሪወች እና ተወዳጆች መሃል የመሆን ዕድሉ የነበረኝ ሴት እሆን በነበረ። ለእኔ የሙያ ብቃት፤ የሥራ ትጋት እና ቅልጥፍና ያግዛሉ በተባሉ መድረኮች ሁሉ እማርበት ዘንድ ሙሉ የዕድል በር የተከፈተልኝ ወጣት ነበርኩኝ። በእኔ ዘመን ዕንቁ ሴት ወጣቶች በርከት ያልን ነበርን። ከሁሉም ግን ለእኔ ይሰጥ የነበረው አትኩሮት እና፤ በእኔ ይጣል የነበረው ተስፋ ሰፊ ነበር። ጎንደር ክፍለ አገር ብቻ ሳይሆን፤ ተወክዬ በሄድኩበት ቦታ ሁሉ ነበር። አርሲ ስመደብ ጢቾ በሠራሁ በሦስት ወሬ ነበር ለክፍለ አገር ኃላፊነት ሪኮመንድ የተደረግኩት። ተሰድጄም የሥራ ኢባሎሽኔ #A + ነው። #አገሬ #ሥራ ነውና። ያውም በበቃ ዲስፕሊን እና በትጋት። ሁሉንም የክብር አይነት አውቀዋለሁኝ። ለዚህም ነው ለውዳሴ፤ የማይደንቀኝ የማልንደፋደፈው ለጭብጨባ ሆነ ተከታይ ለማበራከት። በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ብርቱ ናቸው ብዬ ለማምናቸው በገፍ የሰብዕና ግንባታ፤ ምስክርነት በቅንነት የመስጠት አቅሜም ምንጩ ይኽው ነው። በብዙ ሰው ድጋፍ ላይ ቁብ የለ ሰብዕና ስለአንድ ሰው ሰብዕና የመመስከር #አቅም የለውም። ለምን? ከእነሱ የተሻለ ሰብዕና እንዲወጣ ስለማይፈለግ። ...