ልጥፎች

ከኦክቶበር 16, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ለንጉሥ ታከለ ኡማ ሲባል ግለት በአደባባይ።

ምስል
ያቅለሽልሻል። „በታካች ሰው እርሻ   እምሮ በጎደለው ሰው ወይን ቦታ አለፍሁ“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፬ ቁጥር ፴ ከሥርጉተ©ሥላሴ  16.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።  ለነገሩ እኔ ብዙም አይደንቀኝም ወንበሩ ባዶ ሆኖ ነው ያዬሁት። የዛሬ ሹመት ስንት ቀናት እንደሚሰነበት ደግሞ ወጀብ ይጠዬቅበት። መፈንቅለ መንፈሱ በጉልህ ዛሬ ማዬት ያስችላል። ጉለበታሙ አርሲኛው እና ጉልበታሙ አደዋኛ ጋብቻው የደራ ይመስላል።  ሌላው ሴቶች እኩል በኩል ቁጥር መሆኑ እናትነት አህትነት እርህርህና ሲሉን ጠ/ ሚር አብይ አህመድ ጫካ እንዴት እርህርህና፤ ፋቲክ እንዴት ርህርህና፤ ምላጭ እንዴት እናትንት፤ ጭካኔ እንዴት ደግነት፤ ጋዳይነት እንዴት ጽድቅ ስለመሆኑ ፊት ለፊት በቀዳማይነት  ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ እግዚአብሄርን ሮል ሞዴል አደርገውልን ነው። ወ/ሮ ሙፍርያት ካሜልም ቢሆን ሥራ በዝቶባቸው በፈቃዳቸው ለቀቁ ነው የተባለው። እንደ እኛ በፖለቲካ ድርጅት ለሰራ ሰው እቃ እቃ ጨዋታ ነው። ለጠ/ ሚር ቦታ የሚያሰጉ ሴት እዬሆኑ መጡ፤ አሁን በቅርብ በወሰዱት እርምጃ የለውጡ ኮከብ አንስት መሆናቸው፤ ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው አስፈራን፤ የለውጡን ታሪክ እኛው እንጠቀልለዋለን ቢባል በስንት ጣሙ። አሁንም ድርብርብ ያለ ሃላፊነት ነው ያተሰጣቸው በዛ ላይ ሥሙ "የሰላም"እና ምግባሩ የማይገናኝ ነው።  ለእኔ እንደ ዕንባ ጠባቂ፤ እንደ ሴቶች እና ህጻነት፤ እንደ ሰብዕዊ መብት ኮሚሽን ነው የማዬው። ለውጥ በምለው ወስጥ ያለወን የሴራ ገመድ ምዕራባውያን እንዳያዩት ለመሸበብ ነው። እሳቸው እንዲሙሩት የተፈለገው ተቋማት  የኦሾቲዝ ታሪክ ነው ያላቸው። በሌላ በኩል  እኔ ይህ ዲሞሽን ነው። ዶር አብይ ከሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚ/ር ወደ ኦ