ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 15, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ቢራቢሮ ሥነ - ግጥም። የምወዳትም።

ምስል
ቢራቢሮ ... *** „የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል፤ እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጠላል።“ የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፲፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 15.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ቢራቢሮ። ነይ እሰኪ ዘንድሮ አለፈልግም ከርሞ የለኝም አርምሞ               ሁለመናዬ አሮ               በበቀል ተነክሮ              ቀለም የለሽ ኑሮ፣               ቋሳ ተዘርሮ               መብቴ ተዘሮ                   ሁኛለሁ ደንቆሮ። አንቺ ቢራቢሮ ሕይወት ቢራቢሮ ኑሮ ቢራቢሮ ነፍሴ ቢራቢሮ     ተስፋ ቢራቢሮ አትሁኝ በረሮ አታፍቅሪ ጦሮ።                 ነጠብጣቤ አሮ               ዓይኔም ተማርሮ ቢራቢሮ ...    በበላህሰቦች እንዲህ ም ተወሮ               ከምሾ ተድሮ               ከዋይታ ተዳብሎ። አንቺ ቢራቢሮ ሕይወት ቢራቢሮ ኑሮ ቢራቢሮ ነፍሴ ቢራቢሮ          ተስፋ ቢራቢሮ አትሁኝ በረሮ አታፍቅሪ ጦሮ።               ገሳ ተንተርሶ               ሞረሽን ተንፍሶ                    በቀልን ተቋድሶ፣               ዛሬ ተቀልብሶ               እህህን ተለብሶ። አንቺ ቢራቢሮ ሕይወት ቢራቢሮ ኑሮ ቢራቢሮ ነፍሴ ቢራቢሮ ተስፋ ቢራቢሮ     አትሁኝ በረሮ አታፍቅሪ ጦሮ               ፍሬ ዘሬ ሁሉ ...               .... በምጣድ ታምሶ               አመድ ተነስንሶ              ትብ

ይበቃል ግጥም።

ምስል
ይበቃል። ከሥርጉተ©ሥላሴ 15.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ይበቃል          *** የምን ሽላሽሊውት ? የምን መጓተት ? ጨዋታው ይበቃል አትዋትት። ለአንተ ሲዘንብልህ፣ ለእኔ ያካፋል የሁሉ ፈጣሪ እኩል ያድላል። ያፈለቀልኝን የራሱን ሰላም ያለ ጊዜ መጥተህ አስመነንክብኝ። ጠምቶኝም አያውቅም ምንጩ ከሆ ዴ ነው፣ ከአንተ ጋር መራኳት ጊዜ መግደያ ነው። ቲፍ ብሎ ሞልቶ አንገቴ ድረስ ዕብለት ሃሞት ሆኖ ልቤን አስነከሰ። የምመካው እኔ በአንድዬ ብቻ ነው፣ የአንተማ ክንብንብ፤ ሽፍንፍን - ድፍንፍን   ውስጠ ወይራማ ነው !    ሽበት ምን ያደርጋል ? ... ... ከአናት ላይ መውጣቱ ? ከአልሰገደ በቀር ለወስጠ - ህብስቱ። ክብር ነው ሞገስ፤ ያ ’ ደረ መገኘት ቃል ሕይወትን ዘርቶ ጃኖ ሲሰራበት። ቅልጥ ያለ ቤቱ በጣም የሚያምር ውስጡ ግን አመዳም ለዛቢስ ፈረፈር። እንብኝ አሻፈረኝ አልሻም ብያለሁ የካራንን ህብረት፡ .... ... በ 80 ቀኔ ዘ - ል - የ - ው - ም፤ አለሁ። ከዘለዓለም ቤቴ ከ - ና - አ - ን ስገባ፡ መድህኒቴ አገኘሁ   የተስፋ ዘበኛ። ይቅር ባዩ ጌታዬ ምህረቱን ይልካል ወራዳን ሕሊናን እሱ ያጸዳዳል።   ሥርዬት እያለ እኔ መጨነቄ በፍትሃት ይጸዳል መጨመላለቄ። በቃሽም ይለኛል እሱ ያለ ለታ ተሰፋዬ እያለ ዬኔሁን መከታ።                                                        ·     

ግጥም።

ምስል
„በተንኮልህ ያሳትካቸው አጋንንትና አንተ በአንድነት ወደ ገሃነም ትውርዳላችሁ እና ወዮልህ“ መቃብያ ቀዳማዊ ምዕራፍ ፲፫ ቁጥር ፲፯ ከሥርጉተ©ሥላሴ  15.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ እ ርሾ ነስቶ ሲደነፋ-ሲ ያ ንኮራፋ ዘመን የሰጠው ዶ ፍ                            ሲ ቀር ፍ …                    … ሲ ዘር ፍ                    ሲ ወር ፍ …           … ሲ ሞተል ፍ        ሲ ነድ ፍ … ሲናደፍ    … ሲ ል ፍ ጎርፍ …  የሚወርፍ ዝንቅንቅ -ጥንዝል- ዝንጥለ፤ እንኮፍ- ሸንኮ ፍ ። ·         ተጣፈ  ...  ታህሳስ 4 ቀን 2001 ዓ.ም ሲዊርላንድ ·         ተስፋ መጸሐፌ ላይ ለህትም የበቃ፤ ገጽ 12 ቦታ ካለ ሊዝ የተመራ። ·         እርእሱ ጎርፍ የሚወርፍ ነው። የኔዎቹ ኑሩልኝ። መሸቢያ ጊዜ።

ግድግዳ እና እኔ ሥነ ግጥም።

ምስል
ግድግዳ እና እኔ። „ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሄር እኔ ፈርጄ አጠፋዋለሁ ብሏልን  ከምጽዕት በኋዋለ ግን ለዲያቢሎስ ሥልጣን የለውም“ መቃብያን ምዕራፍ ፲፫ ቁጥር ፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 15.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ·       ወግ ቢጤ። ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት አላችሁልኝ። ትናንት ብቅ አላልኩም፤ ሚስጢረ አዲስን ገለጥለጥ ለማድረግ ፈርቼው አይደለም።  እኔ የሥላሴ ባርያ ከፈጣሪያ በታች እምፈራው ህግ ብቻ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ከፖለቲካ ውጪም ህይወት አለ። ነፍስም አለች። መኖርም አለ በዛ ተከርም መሥራት ያስፈለጋል። የሆነ ሆኖ ዕውነት በሌለችበትም ስለ እውነት ጮኼለሁኝ። አትኩሮት ሊሰጣቸው በሚገቡ ወገኖቼንም ቢሆን እንደ እኔ ደፍሮ የሚጽፍ የለም። ስለ ወገን ደግፍሮ በቅንነት፤ በትጋት እና በተከታታይ መጻፍ አንዱ የመጻፍ ባህሌ ነው። ይህ ደግሞ  በእኛ የለም። ስለ ሌላው ወገን መመስከር፤ ስለ ሌላው እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ የሚፈራ አምክንዮ ነው። ለዚህ ነው ቃለ ምልልሶች በመቁኑን፤ በደንበር፤ በወገንተኝነት፤ ወይንም አቋሙን ለማጋለጥ ሲታሰብ ብቻ ታቅዶ ሲከውን የምታዩት። ከእኔ በላይ የሚበልጥ መፈጠሩን መመስከር ወይንም ስለዛ ነፍስ መሞገት አውቀን የተውነበት ምክንያቱ ድምቀትን፤ እውቅናን ከራሳችን አልፎ እንዳይሄድ ስለምንሻ ብቻ ነው። የኢጎ እና የምቀኝነት እስረኞች ነን። በእኔ ቤት ግን ይህ የለም። ወደፊትም ካለምንም ተዕቅቦ ለእኔ ዕውነት ነው በምለው አምክንዮ ዙሪያ ይጣፋል። ያልተጣፈበት ምክንያት አቀባበሉን ድምቀት ከልብ የሚፈቅደው  የኢትዮጵያ መንግሥት፤ የአዲስ አባባ የከንቲባ ቢሮ በተለዬ ሁኔታ እና ወገኖቼ ፈቃድ አላቸው የኦነግን አንድ ክንፍ አቶ ዳውድ ኢብሳን ለመቀበል።  የፈቀዱትን እስኪ