ልጥፎች

ከዲሴምበር 2, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ዬሀሮ አዲስዓለም ጉዳይ።

ምስል
  ·       ዬሀሮ አዲስዓለም ጉዳይ።   ይድረስ ለማከብረወት ለዶር ዳንኤል በቀለ ዬኢትዮጵያ ሰባዕዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር።   አዲስ አበባ   ድጋሜ አቤቱታ።   በ 30/11/2022 ዕለት አመልክቻለሁኝ። ከተለያዩ የወለጋ አካባቢወች የተፈናቀሉ ከ 30 -45 ሺህ የሚደርሱ የአማራ ተፈናቃዮች እጅግ በሚያሳስብ ሁኔታ ከበባ ውስጥ ናቸው። ይህ ሌላ እራስን የማዳን እንቅስቃሴ ከተለወጠ የማይበርድ እሳት ያቀጣጥላል።   አስፈላጊ እና ሴንሲቲብጉዳዮች ሲገጥሙ ተቋመወት እንደምን አፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስድ አውቃለሁኝ። ለዚህም ጉዳይ ከምንም ነገር ዬቀደመ እርምጃ ካልተወሰደ ከቁጥጥር ውጪ ሊሆን ይችላል። ቁጥሩ በትናንቱ የጥዋት መረጃ ላይ ኢትዮ ኒውስ 45 ሺህ ብሎ የዘገበ ሲሆን ትናንት ከሰዓት መረጃውን አሻሽሎ ከ 30- 45 ሺ ብሎ ነበር። ዛሬም ተቀራራቢ ግምቱን ዘግቧል።   ኢትዮጵያ ውስጥ የአማራ ነፍስ የወፍ ያህል ክብር እንደሌለው ባውቅም ቢያንስ ለእርስወ ማመልከት የተሻለ ሆኖ ስላገኜሁት ደጋግሜ በትህትና ማሳሰብ ግድ ብሎኛል።   በኦሮምያ ያለመከሰስ መብታቸው ተረግጦ ስለታሰሩ ዬከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች በአፋጣኝ በወሰዳችሁት እርምጃ ፍትህ ቀና ብላለች። በአማራ ህዝብ የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ወከባ፣ ማሳደድ፣ ማፈናቀል፣ የስጋት ጫናስ ????   በዬዕለቱ ዬአማራ ደም ይፈሳል ዛሬም ዬስድስት ንፁኃን ነፍስ እንዳለፈ ከኢትዮ ኒውስ አዳምጫለሁኝ፣ ባለፈው ቀንም ከ 20 በላይ ???? እስከመቼ ተቋመወት ግል