ክቡር ተዋናይ ኪሮስ ኃ/ሥላሴ።
ለባለግርማው የጥበብ ክህሎት ለተዋናይ ኪሮስ ኃ/ሥላሴ ምህረቱን ይላክ አዶናይ „አሜን!“ ከሥርጉተ ሥላሴ 25.05.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) „ምንም እንኳን በለስም ባታፈራ፣ በወይን ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፤ የወይራ ሥራ ቢጓደል፤ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፤ በጎችም ከበረቱ ቢጠፉ፤ ላሞችም በጋጥ ውስጥ ባይገኙ፤ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመዳህኒቴ አምላክ ሐሴት አደርጋለሁኝ። ጌታ እግዚአብሄር ሃይሌ ነው። „አሜን!“ ይሁንልን! ይደረግልን! (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ከቁጥር ከ፲፯ እስከ ፲፰) የውስጥ መስመር ... ጥበብ ዘር የላትም፤ ጥበብም ፍቅር ናት፣ ጥበብ ቅርጽ የላትም፤ ጥበብ ብርሃን ናት፣ ጥበብ ፎርም የላትም፤ ጥበብ ነባቢት ናት፣ ጥበብ ቀለም የላት፤ ጥበብ የሁሉም ናት፣ ጥበብ መኖርም ናት መልካም ሐዋርያ ትርሲታዊ ሰናይ፣ ለፈቀዳት ሁሉ የምታደላድል የመንበር የበላይ። · ጥበብ እንዲህም ናት … የትህትና መዝሙር የአገልግሎት ዝክር የድካም ዕንቢልታ የጥንካሬ በር። መች ሆና ስታውቀው ጥበብ ወረተኛ የትውፊት ውሃዋ የዓይን ዘበኛዋ። · ጥበብ ፊት አትሰጥም … ጥበብ አይደለችም የጉድፍ አንቀልባ የልዩነት ዳባይ ጥበብ ጎታ የላት ለኩፉኝ እኩይ። ጥበብ ፊት አትሰጥም ለስንኩሉ ገደል ለሃሰት ቃል አባይ፤ ጥበብ አይደለችም የክፋት ኩነኔ የክፉ ላብ ብካይ። ሰነፍ ጥበብ የለች አልተፈጠ