ልጥፎች

ከኖቬምበር 15, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

#እኔን። በዛ በመተማ ቃጠሎ እያገለገለ በግፍ ታግቶ የተገደለ ታናሽ ወንድማችን ነው።

ምስል
  #እኔን ። በዛ በመተማ ቃጠሎ እያገለገለ በግፍ ታግቶ የተገደለ ታናሽ ወንድማችን ነው።      #እናትህን #አያድርገኝ ። #አዳኝ #ታድኖ እንደምን #በጭካኔ #ይገደላል ???? ተጎጅውስ ማህበረሰቡ አይደለምን??? "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ጭንቅን #ተጋሪወች ፤ #መፍትሄም #አመንጭወች #አዛኞች እና #ተንከባካቢወችን የኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያወችን #ማን ይሆን ያላቸው? የህክምና ባለሙያወች አገር አቅኝም ናቸው። የሰው ልጅ አለ በሚባልበት ቦታ ሁሉ በቀን ሃሩር፤ በሌሊት ግርማ ሞገሱን ታግስወ በቅንነት የሚተጉ ሊቀ ትጉኃን።    እንደዚህ በየሄዱበት እያገለገሉ ደመ ከልብ ሆነው የሚቀሩ አሳዛኝ ፍጥረቶች ሆኑ። በስንት ድካም፤ በስንት ልፋት የሚገኝ ሙያ እና የጥረት ስኬትም ለባሩድ ጭካኔ ተዳረገ። አገልግሎቱ ቢቋረጥ በዚህ ጭንቅ ጊዜ ምን ትጠቀሙ ይሆን? የቻለ ወደ ተሻለ ቦታ ሄዶ እንዳይታከም ሁሉ ነገር ዝግትግት ብሏል። ማህበረሰቡ ለዓይኖቹ ስለምን ጥበቃ አያደርግም በየተራ????ለምንስ በጋራ አይመክርም??? መፍትሄ ፈልጉ እባካችሁን???   ለሰማቱ ሊቀ ትጉኃን ለመላ ቤተሰቡ ሁሉ መጽናናትን እመኛለሁኝ።    ሥርጉትሻ 2025/11/2025   እግዚአብሄር አምላክ ሁሉ ይቻለዋል እና ሰማያዊ ርትህ ይስጥበት።    ውቦቹ ውዶቹ ቤተ ቅንነት እስኪ ደህና አርፍዱ። ቸር ያሰማን። አሜን።   /// ከመተማ ኮምኒኬሽን ያገኜሁት ነው። ይህ ግን መፍትሄ አይሆንም። ሌላ ነፍስ አድን የተደራጄ ጥበቃ ለባለሙያወች ሊደረግ ይገባል። መኖር ይፈትናቸዋል። ደግሞ እንዲህ ህይወታቸው ይነጠቃል። " ………በግፍ እና በአሰቃቂ ሁኔታ ሂወቱን ለተነጠቀው ...

ብጹዑ አባታችን በመከራችን ሁሉ ቀድመው የሚገኙ #ሐዋርያችን ናቸው። ማገዶነት ለብጹዕነታቸው ብርቃቸው አይደለም። የኖሩበት ነው።

ምስል
  ብጹዑ አባታችን የመከራችን ሁሉ #ሐዋርያችን ናቸው። ማገዶነት ለብጹዕነታቸው ብርቃቸው አይደለም። የኖሩበት ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።     በዛ ግራጫማ ህወሃታዊው ዘመን እንኳን ሳይፈሩ፤ ሳያርዱ ከተከፋ ልጆቻቸው ጋር ሆነው #ግማድ የተሸከሙ፤ አንደበተ #ርዕቱ ፤ ብቁ እና #ጥንቅቅ ያሉ ስጦታችን ናቸው። እንደምን ያለ #እብድ ዘመን እንደሆነ ትናንት አየሁኝ። በብፁ አባታችን አቡነ አብርኃም ፎቶ ላይ #ኤክስ ምልክት እንደምን ያለ መዳፈር ነው? እንደምንስ ያለ ህግ መተላለፍ ነው? ክርክር አላስፈለገኝም። መራራ ስንብት ነው ከወዳጄ ጋር ያደረኩት።    ከዚህ ቤት፤ ከቤተ - ቅንንነት እንኳንስ #ሐዋርያትን ማንም ሰብዕ፤ እንሰሳ፤ ዕጽዋት ሳይቀር የሚከበርበት ነው። የሰብዕን ፎቶ #መዘቅዘቅ ፈጽሞ #አይፈቀድም ። በማንኛውም ሰው ላይ የኤክስ ምልክት ማድረግም የተከለከለ መንገድ ነው። እኔ ሥርጉተ ሥላሴ፤ ሰብለ ሕይወት የማንን ጎፈሬ እማበጥር ይመስላችኋል። ነገረ ትውልድ ትርታዬ ነው። ስለ ትውልዱ ስጽፍ በፆም በጸሎት በመጠሞን ነው። ከልጆች መፃህፍት ቅንጣት ዝበት አታገኙም። ልጆቻችን እኛ ባለፍንበት ትርኪ ምርኪ፤ ግፋፎ ሁነት ማለፍ የለባቸውምና።   ስለሆነም ከባህላችን ውጭ የሆኑ ፆታ ነክ ጉዳዮን ተደፍረው ከዚህ ቤት አይለጠፋም። ካገኜሁም አይቀሬው ስንብት ይሆናል። ሌላው ቀርተው በቋንቋችን ውስጥ ያሉ ጸያፍ የሆኑ አገላለፆችን መጠቀም እንኳን አይፈቀድም። አማርኛ ቋንቋ #ዲታ የለማ ቋንቋ ነው። እንደ ጀርመንኛ ቋንቋ።    አንድ ፊደል ብቻውን ከትርጉም አልፎ ዕጣ ነፍሱን #ቅኔን ይቃኛል። ዕርዕስ መሆን ይችላል። #ቃ የሚለው አንድ ፊደል ዘርፈ ብዙ ትርጉም አለ...

የኢትዮጵያ ጤና ሚር ያወጣው አዲስ መግለጫ።

ምስል
 

#ወይ #ጢቾ? #የጢቾን የቀደመ ጥልቅ #ተፈጥሯዊነት #አቤቱ #የኦህዴድ #ሊቃናት #መልሱልን።

ምስል
  #ወይ #ጢቾ ? #የጢቾን የቀደመ ጥልቅ #ተፈጥሯዊነት #አቤቱ #የኦህዴድ #ሊቃናት #መልሱልን ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ። አሜን።     #ጠብታ ።    ከየት እንደምጀምር አልውቅም። እኔ ለምለሙን ጢቾ እማውቀዋለሁኝ። ጢቾሻን እኔ የማውቀው ግን በዚህ አሰቃቂ ግፍ እና ሰው ጠል በሆነ፤ መስቀልን ገፊ #የማፈናቀል ታሪክ አልነበረምና ከበጎው ከናፍቆቴ ልነሳ። በአሜሪካኖች ሃሙስ በእኛ አርብ ነበር አደባባይ ሚዲያ ካርታውን ሲያቀርብ ጢቾም እንዳለበት የተገነዘብኩት። ቀደም ብሎም ምስራቅ አርሲ የሚል ጉግል ላይ ፈልጌ በጉልህ ላገኜው አልቻልኩም።    በእኛ አርብ ዕለት ግን አደባባይ ሚዲያ በጉልህ ሲያወጣው ማህጸኔ እንደ ዱባ ነው የተቀረደደው። አደባባይ ሚዲያ ገረጭራጫ ሚዲያ አይደለም፤ በስሜት ግንፍል ግንፍል የሚልም ሁነትም በርክቶ አላይበትም። በቃላት አጠቃቀም፤ በቅደም ተከተል አመክንዮወች፤ ሃሳብን በልዩነት አቻችሎ በማስተናገድም #ስክነት ስለማይበት በመደበኛ እከታተለዋለሁኝ። የቲሙ የሃሳብ ፍልሚያም ለትውልድ የመቻቻል ቀጣይነት አቅጣጫ ጠቃሚ ይመስለኛል።   "የጊዜ ባለቤት" ብሎ አምላካችን አመስግኖ የሚጀምረው የመምህር አቤል ጋሹ በር ከፋች ቃለ ህይወትም ይናፍቀኛል። #ይጠራኛልም ። ያው ልጅ ተክሌ እና እኔ ስንሟገት ነው የኖርነው፤ በቀረበበት ሚዲያ ሁሉ ናፍቄ አዳምጠዋለሁኝ። ቅንም ነው። አይሰስትም ትጉኃንን አጉልቶ ለማውጣት። ለኮሚኒቲውም ነፃ አገልጋይ ነው።    ባለቤት አልባ እስረኞችን ኢትዮጵያ ሲሄድ በአካል ያያል። ቀጠሮ ካላቸው በአካል ይገኛል። ሁነኛ #ተስፋዬ ነው። እኔ ኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ እንዲኖራት ፈጽሞ አልሻም እና ለእኔ በኽረ ጉዳዬ ነው...