ልጥፎች

ከጁላይ 4, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

እነ ቢቢኤን "ሲሮጡ የታጠቁት ሲሮጡ ይፈታል።"

ምስል
„የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል!“ ከሥርጉተ ሥላሴ 04.07.2018  (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ) „በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ ነው፤  መንገዱም ትልቅ ነውና፤  ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤  ወደ ህይወት የሚወስደው ደጁ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና፤               የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።“        (የማቴወስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፫ ቁጥር ፲፬) እንደ በር። ከቶ እንዴት አላችሁልኝ ክብረቶቼ። አሁንም ትዝብቴን ላጋራችሁ ነው።  ጠ/ ሚር አብይ አህመድ በባዕለ ሹመታቸው ባደረጉት ንግግር ላይ ሰፊ ቅሬታ ካሰሙት ውስጥ እንደ ሚዲያ ቢቢኤን እንደ የራዲዮዎ ጋዜጠኛ ደግሞ አቶ ሳዲቅ አህመድ ነበር። ያው "የድምጻችን ይሰማ" ቤተሰብ ስለነበርኩኝ ዜናው አዲስ ስለሚሆን ተግቼ እከታተለው ነበር። በመደበኛ። የቢቤኤን ጋዜጠኛውን አቶ ሳዲቅ አህመድ ደግሞ ከማከብራቸው ነፃነትን ከሚሹ ቅኖች እንደ አንዱ አዬው ስለነበር ሳነበው ደነገጥኩኝ።  እርግጥ ነው ራዲዮ ጣቢያው ገና ከውጥኑ ጀምሮ ነበር  ጠ/ ሚር አብይ አህመድ ለእጩ ጠ/ ሚርነት ሲወዳደሩ ነበር ወጮፎውን ያወረደው። እስከ ደነግጥ ድረስ። አንድ ለውጥ ሲመጣ የለውጡ ቤተኞች ደስ ሊለን ሲገባ የሃይማኖት ሰበዝ መሰበዝ ተጀመረ። እኔም ላጣው ስላልፈለግሁኝ ሥሙን ጠቅሼ ጻፍኩኝ። የሚገርመው ለቢቢኤን ጋዜጠኛ አቶ ሳዲቅ አህመድ የሹመት ንግግር ማለት ፖሊሲ መስሎታል።  ወይንም የሥራ ዘመን መከወኛ ሪፖርትም መስሎታል፤ ወይንም መጸሐፍ እንዲሆን ፈልጓል። አንድ የሹመት ንግግር የፖሊሲ ሃሳብ ሊይዝ ይችላል፤ አቅጣጫ አመላካችም ሊሆን ይችላል። ግን ለእነዛ በቀጣይ በህግም በዝርዝር የአፈጻጻም መመሪያ ጊዜ ጠብቆ የሚ

የጋዜጠኛ መሳይ መኮነን የዱብ ዕዳው ዋጋ አሰጣጥ ፉርሽነት!

ምስል
የጋዜጠኛ መሳይ መኮነን ደርሶ ዱብ ያለ ለዶር አብይ አህመድ ዋጋ የመጨመር ዕሴቱ ፉርሽ ነው። መናጆ መሻት ነው። ከሥርጉተ ሥላሴ 04.07.2018  (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ) „ጌታ ሆይ አድነን ጠፋን እያሉ አስነሡት።  እርሱም እናንተ እምነት የጎደላችሁ ስለምን  ትፈራላችሁ? አላቸው። ከዚህ በኋዋላ ተንሰቶ  ነፋሱንና ባሕሩን ገሠጸ፤ ታላቅ ጸጥታም ሆነ።“ (የማቴወስ ወንጌል ምዕራፍ፰ ቁጥር ፳፮ ) ·        መነሻዬ ይሄ ነው። https://www.satenaw.com/amharic/archives/59937 „ ሰውዬው ተራ ጀብደኛ ነው ( መሳይ መኮነን July 3, 2018 ) እንዴት አለህ ጋዜጠኛ መሳይ መኮነን? ሰላም ነው? በቅድሚያ እንኳን ለዚህ አበቃህ እላለሁኝ። „እንዳያማም ጥራው እንዳይበላም ግፋው“ በነበረው የህሊና ምርትህ ውስጥ በጠ/ ሚር አብይ ጎን ስለመሰለፍ የሚያመለክት ይመስላል ጡህፍህ። ተቆርቋሪነቱ ለዶር አብይ ነብስ ያደላ ይመስላል። እስኪ ከዘለቀ የሚታይ ይሆናል። የወግ ገበታ። ውዶቼ። የጋዜጠኛ መሳይ ጹሁፍ ዱራኛ ነው። የጠገነ ስለሚመስለው „ጤና አዳም“ ሁልጊዜ በድምጽ ሽፋን ይሰጠዋል። በዛ ውስጥ ያሉ ጉዳዮች ግን እንዳለ የሚለቀቅ አይደለም፤ አልነበረምም፤ አፍሶ መልቀም፤ ለቅሞ ማፈስስ፤ አፍርሶ መጠገን፤ ጠግኖ ማፍርሰ የተመለደ ጨዋታ ነው በኢትዮጵያ ፖለቲካ። ለዛውም ምን የፖለቲካ አቅም እና ቁመና ሳይኖር፤ የተጀመሩ ጥረቶችን ደግፎ ከመቆም በሰማይ መና መማለል የፖለቲካ አስተሳስብ ድህነት ነው - ለእኔ። እኔ ሲኖረኝ ብቻ ነው ባለኝ ነገር መመካት የምችለው እናም የተሻለ ቦታም ደረጃም በቀጣይ እምመኛው። አገር ቤትም ውጪም ያሉት የፖለቲካ ድርጅቶች ይታወቃ