ልጥፎች

ከ2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

#ዛሬን #ለመስኪ! #ብዙዬ #የብዕር "አንጋቿ" ውዴ ክብርት መስከረም አበራ እናትም ነሽ። #ታድለሽ!

  #ብዙዬ #የብዕር "አንጋቿ" ውዴ ክብርት መስከረም አበራ እናትም ነሽ። #ታድለሽ !   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   እናት መሆን የቻልሽው መስኪ እንኳን ለድንቁ፤ ለውቡ፤ ለበረከት ቀኑ የዓለም ዓቀፍ እናቶች ቀን ደረስሽልኝ። አንቺ ብዙ ነሽ። በቋሚነት በትንታጓ ብዕርሽ እደነቅም ነበር። የዘሐበሻ እና የሳተናው #ቋሚ #አምደኛ ሁለታችንም በነበርንበት ጊዜ ሁሉ ጽናትሽ ይደንቀኝ ነበር። አገር ቤት ሆኖ ያን መሰል የሃሳብ ሙግት አቅምሽ ይደንቀኝ ስለነበር አንድ ቀን ኢሜል ፃፍኩልሽ። ፈጣሪ አምላክ #ቸርሽን ያሰማኝ ዘንድ እለምነዋለሁኝ። የማይገኜው ዕፁብ የእናትነት ጸጋ ፈጣሪ ስለሰጠሽ ይመስገን። አሜን።   የማከብራችሁ የአገሬ፤ የዓለም እናቶች ሆይ!   እንኳን ለብርኃነ - ለዓለም ዓቀፋ ክቡር ቀን ለእናቶች በዓል #ደረሳችሁልን ። እናንተ ኃላፊነት እና ግዴታችሁን ባትወጡ እኮ ምድር ወና ትሆን ነበር። ስለሆነም ለሰጣችሁን የትውልድ #በረከት ልዩ ምስጋናዬ በያላችሁበት ይድረስ።   #እናታዊነት የደግነት መንክርነት ነው።   እናትነት የእናትን ተግባር መወጣት ስለሆነ፤ በልጆች ጉዳይ ኃላፊነት የወሰዳችሁ የረባ ዕውቅና ተሰጥቷችሁ የማያውቀው #አባቶች ፤ #ታላቅ እህት እና ወንድሞች፤ #የበጎ አድራጎት ያቋቋቋማችሁ #ደጋጎች ፤ #በማደጎ - በማር ልጅ ኃላፊነትን ፈቅዳችሁ የወሰዳችሁ ሁሉ እናትነት ተግባር እና ምግባር ነውና እና እንኳን ለዚህ #ቅዱስ ቀን በሰላም ደረሳችሁ።   ዕለቱ የደግነት፤ የርህርህና፤ የዕውነተኛ ሰውኛ ቀን ነውና ስናስበው በውስጣችን ሰፊውን ቦታ ይዞ የሚገኜውን #ክፋ ሃሳብን በማጽዳት ቢሆን ምርጫዬ ነው። የቻላችሁ ደብረብርኃን ቅር...

ዓውሏዊ

 ዓውሏዊ #ተደባዳቢ የሃሳብ ገጠመኝን ማስከን ያስፈልጋል። ብስጩ የሆነ #ቦክሰኛ ንፋስም ይገጣማል፤ ወይንም መንፈሳዊ አቅምን ዘልቆ ገብቶ የሚሰባብር #ጦሮም ይገጥማል፤ ከዛ ጋር የማን ደም ፈሰሰ ከመባባል አረጋግቶ እንዲሰክን ማድረግ በእጅጉ ያስፈልጋል። ከአውሎውም ይሁን ከተበሳጬ የተለያዩ የንፋስ ዓይነቶች ጋር የማን ደም ፈሰሰ መባባል አይገባም። መሃል ላይ ያሉ፤ አክሰሱ ያላቸው #ታዳጊ ወጣቶች ይኖራሉ። እነሱ መንፈሳቸው #ለጋ ስለሆነ የሁለቱን ብስጩ የንፋስ ገጠመኝ የመሸከም አቅም ያንሳቸው እና የሥነ - ልቦና መሰበር ሊገጥማቸው ይችላል። ወጀብ ሲኖር ዝቅ ብሎ ማሳለፍ ፍርኃት ሳይሆን ብልህነት ነው። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ሥርጉ 06/05/026

#ኢትዮጵያዊነት በራስ መተማመን ነው። (Confidence) (Vertraun) ነው። #ኢትዮጵያዊነት ተፈጥሮኛ ዲፕሎማትም ነው። እኛ ነው ልኩ መሆን ያቃተን።

  #ኢትዮጵያዊነት በራስ መተማመን ነው። (Confidence) (Vertraun) ነው። #ኢትዮጵያዊነት ተፈጥሮኛ ዲፕሎማትም ነው። እኛ ነው ልኩ መሆን ያቃተን።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   ማህበረ ትህትና እንዴት አደራችሁ? እንደምን አረፈዳችሁ? እንዴትስ ዋላችሁ? ሁለት ተወራራሽ ዕርዕስ በአንድ ጭብጥ።   #ለአፍታ ።   እስቲ እኛን በእኛነት፤ እኔ በእኔነት፤ ሁላችንንም በሁለመናነት አመጣጥኖ፤ ቀምሮ፤ መጥኖ ያበጀንን ኢትዮጵያዊነትን መርምሩት። ቅጥልጥል፤ ቀንድ እና ልጥፍጥፍ የሚያሰኛቸውን ወገኖቼን አይመለከትም ጥያቄው። እንደ ሰው አስበን፤ ሰው ሆነን እንዘልቅ ዘንድ ውስጣችን እራስ እጉሩ ያሰበለ እንዲሆን ያደረገውን ጀግናውን ማንነት ከህሊናችን ሁነን እንሰበው።   #አይደፈሬው ደፋሪውን ያስተምራል።   ሁልጊዜ፤ ለምንግዜም ኢትዮጵያዊነት ኦክስጅናችሁ ሲሆን፤ የትኛውንም የፈተና ጋራ የመበገር አቅም ታገኛላችሁ። ኢትዮጵያዊነት የተደራጄ ተፈጥሯዊ የአቅም ልዩ መክሊት ነው። በኢትዮጵያዊነት ውስጥ የተመጣጠነ፤ ህብራዊ የሆነ ቀለማም መሳጭ ጸጋ አለ። ረቂቅ የሆነ በራስ የመተማመን አቅም አለ። ይህ አቅም ዩንቨርስቲ ገብታችሁ ብትማሩት የማታገኙት እንደ ላሊበላ አለት ጸንቶ የሚያጸና፤ ረግቶ የሚያረጋ #የመሰጠት ዲካ ነው።   #እርግጥ ነው ኢትዮጵያዊነት ተፈሪ ማንነት ነው። በልኩ መሆን ሲሳን ይፈሩታል። ይገባልም።    እርግጥ ነው ኢትዮጵያዊነት የሚቀናበት ማንነት ነው። ኢትዮጵያዊነት በጥበብ ውስጥ የሚዘልቅ የዊዝደም ጎዳና ነው። በኢትዮጵያዊነት ውስጥ መንፈስ ሲቀማጠል ይደለዋል። ለምን? እርግጠኛ የሚያደርግ ልዩ ኢነርጂ ስላለው። ኢትዮጵያዊነት ...

#ውሃዬ………

  #ውሃዬ ………   "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   ኢትዮጵያ ~አገሬ ስስቴ ~~ናፍቆቴ የእኔ ~~~መጠሬዬ ክብሬ እና ~~~~ኩራቴ ንባቤ ~~~~~ትርጉሜ መንፈሴ ~~~~~~ሚስጥሬ ቀደምቷ ~~~~~ግርማዬ ጠይሟ ~~~~ዕንቁዬ ቡኔዋ ~~~~ቡናዬ እናት ~~~ሃይማኖቴ #ዓናቷ ~~ሐሤቴ ውድዬ ~ህብረቴ ቅኔዬ ~~ድጓዬ ኢትዮጵያ ~~~አገሬ የአፍሪካ ~~~~ፊደሌ መዝሙሬ ~~~~ሃናዬ ኃይሌና ~~~~መክሊቴ የእኔ ~~~~~ስጦታዬ ንባቤ ~~~ማዕረጌ ማርዳዬ ~ውበቴ ናርዶሴ ~~ሳባዬ መንዙማ ~~~ህብስቴ ሁሉዬ ~~~~~ዕውቀቴ አንች ነሽ ~~~~መንገዴ ፍልስፍና ~~~~ማዴ ሉሲዬ ~~~ዝናዬ ውዳሴ ~~ድርሳኔ ቅንዬ~ ´መቤቴ የተስፋ ~~መርከቤ የህቅታ ~~~ምግቤ የመኖር ~~~ቋንቋዬ ስዋሰው ~~~ውሃዬ ጠሐዬ ~~~~ብዙዬ ዘውዴ ~~~~~ጉልላቴ እቴጌ ~~~~ልዕልቴ ህብስቷ ~~~~ሥህኔ የእኔ ~~~የእኔ! የዕውነትም ~~ገዴ ለመርህም ~ቅርቤ የዕድምታ ~~ክቤ የአቋም ~~~ተቋሜ የሞራል ~~~~ዘቢቤ የጽናት ~~~~ግማዴ።   ፈጣሪዬ ሆይ! የማንነት ቀውስ ድርሽ እንዳይልብኝ በሙሉ የራስ መተማመን ሰብዕናዬን ገንብታ ያሳደገችኝ ልዕልት ኢትዮጵያን ጠብቅልኝ። አሜን።   ተፃፈ ~ ዛሬ 06/04/026 ሰዓት ~~ 08.20   ሥርጉተ©ሥላሴ። Sergute©Selassie. Selassie©Selassie.   #ኢትዮጵያዊነት #ከመፈጠሩ #በፊት #ፈተናን #አሸንፎ #የተፈጠረ #ሚስጢር ። See less

#ምርጫው ቢራዘምስ? መሪው የምርጫ ምልክት #ነዶ ምርጫው ታስቀጥል ይሆን? ብታራዝመው አይሻልህምን?

  መሪው የምርጫ ምልክት #ነዶ ምርጫው ታስቀጥል ይሆን? ብታራዝመው አይሻልህምን?    ግን ቆረጠ #ብልፄው 7ኛ አገራዊ ምርጫውን ለመፈጸም?   አገራዊው፤ አህጉራዊው እና ሉላዊው ሁነት ሲታሰብ ምርጫን መፈጸም ወይንስ ማረዝም የቱ ይቀል ይሆን?   ማራዘም ላይ ተጫኝ ሁለገብ ችግሮች አይለዋል። ገና ሳይጀመር ሞት አለ። ራስ ጋይንት ላይ አሳዛኝ ሁኔታ ነው ያለው። ሞቱ ከምርጫ ጋር ተያይዞ ነው።   ማስጠንቀቂያውም እንዲሁ ነው። በከፋኝ ዱር ቤቴ ባሉ ታጣቂወች በኩል #ዋ ! ብትመርጥ// እጩ ሆነህ ብትመረጥ፤ በብልፄው በኩል ዋ! #ባትመርጥ ባትሳተፍ /// እጩ ሆነህ ባትቀርብም ህዝባችን ወከባ ላይ ነው። ጭንቅ ላይ።    #ምርጫው ቢራዘምስ?   #ግን ጉዳዩን ለመንፈቅ ወይ ለ፩ ዓመት ምርጫው #ቢራዘምስ ? አልኩኝ እኔው። ርጋታ የለም። የተረባበሼ መንፈስ ነው ያለው። ውጥረቱ የመንፈስ አና ብሏል። ከኑሮ ውድነቱ፤ ከሰላም እጦቱ ጋር ምርጫ + ጫን ተደል ጭንቀት ተሸክሞ ምጥ ላይ ነው????    በነገራችን ላይ ዴሞክራሲን ባለመለሙ፤ ሰላማቸው በተረጋጋ አገሮች እኮ ምርጫ ልብ ያንጠለጥላል፤ ዘናም ያደርጋል፤ ፋክክሩ ሲጦፍ ትዕይንት ነው።    "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   እኔ ምርጫ መብት ነው ብዬ አምናለሁኝ። መምረጥም /// መመረጥም የመብት ቅኔ ናቸው። ዕድሉ ባያፈስ የሚመለከታችው ሁሉ ቢሳተፋ፤ ሁሉም ቢሳተፋ ጥሩ ነው።   #ግን አጤ ሆርሙዝ ሁለገብ ተጨማሪ ራህብን አውጇል፤ የቤርሙዳ ትርያንግል ያህል እዬከበደ ነው። ከስምምነት ቢደረስ እንኳን የተረጋጋ ሁነት ለመፍጠር ዘለግ ያሉ ወራቶች ያስፈልጉታል እዬተባለ ነው። የኃይል አሰላለፍም ብወ...