ጨረቃ ክንፍ አውጥታ ሰማይ ላይ ብትበር፤ ጸሐይ በሠረገላ ወደ ምድር በሚያስፈራ ግርማ ብትመጣ፤ የሰማይ ታምራት እና ገድላት በምድራችን ላይ ቢገለጥ፤ ህወኃት ኢትዮጵያን የመምራት #ዕድል ፈጽሞ አይኖረውም።
ጨረቃ ክንፍ አውጥታ ሰማይ ላይ ብትበር፤ ጸሐይ በሠረገላ ወደ ምድር በሚያስፈራ ግርማ ብትመጣ፤ የሰማይ ታምራት እና ገድላት በምድራችን ላይ ቢገለጥ፤ ህወኃት ኢትዮጵያን የመምራት #ዕድል ፈጽሞ አይኖረውም። "እናንተ ሰነፎች ልበ ቢሶች፤ ዓይን እያላችሁ የማታዩ፤ ጆሮም እያላችሁ የማትሰሙ፤ ህዝብ ሆይ! ይህን ስሙ። በዕውን እኔን አትፈሩምን? ከፊቴስ አትደነግጡምን?" (ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፳፩ - ፳፪) #ምዕራፍ ፲፱። #ጠብታ ። ተዘርዝረው የማያልቁ የሰው ልጅ የጭካኔ ዓይነትን ተቀብሏል ህዝብ በህወሃት። ያ የግፍ፤ ያ የስቃይ፤ ያ መተንፈሻ ያልነበረበትን የጭካኔ ዘመን መላ የኢትዮጵያ ህዝብ በወረፋ ቢደርሰውም በስሜን ጎንደር የደረሰው፤ በአዛውንት #ተጋሩ ዕውነት መስካሪነት የተፈጸመው አሰቃቂ ሰቆቃ ዕንባን ሰማይ አዳመጠ። መለሰም። ህወሃት ፈቅዶ እራሱም ድምጽ ሰጥቶ ሁለት ድምጽ ብቻ አግኝቶ ሥልጣነ - መንበሩን ሲለቅ፤ ከዚህ በላይ ዲስፕሊን የለም በማለት ውሃ በቀጠነ ህወሃትን አጀንዳ ያደረጉ ሚዲያወች ይሁን ግለሰቦች ሲሞግቱት እኔ እንደ ቋሚ ሞጋችነቴ ጸጥ ብዬ ነበር እምመለከተው። የህወሃት እና የብልፄ ጦርነት ዱብ - ዱብ ሲልም፤ #ተው ከማለት ውጪ አንዳችም ቃል ብዕሬ አውጥታ እንድትናገር አልፈቀድኩም። እንዲያውም "መጤ፤ ጸጉረ ልውጥ" በሚሉ አገላለፆች ቅሬታዬን ጽፌያለሁኝ። የተገባ አልነበረም። ይቅርታም በይፋ ሊጠየቅበትም ይገባል። ለይቅርታ ቅድመ ሁኔታም ቀጠሮም ስለማያስፈልገው። ሰው በአገሩ፤ በባዕቱ - "መጤ፤ ጸጉረ ልውጥ" ፈጽሞ ሊባል አይገባምና። በጦርነቱም ወቅት ጉዳቱን ከዓለም ዓቀፍ ሚዲያወች ብቻ የማገኜውን የግራ ቀኙን ሰብአዊነት...