«ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ « እርዕሱ የፋና ነው።

 

«ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ « እርዕሱ የፋና ነው።
"መግለጫ" እንደምን እንዳሉት አላውቅም።
 
 
#ማብራሪያ#ወቅታዊ መረጃ ቢባል የተሻለ ይመስለኛል። መግለጫ
የውሳኔ ሃሳብን የሚይዝ ነው። ይህ ግን የሚዲያ ማብራሪያ ነው።
ኮሚሽኑ ምን ላይ እንዳለ፤ ቀጣይ አቅጣጫው ምን ሊመስል
እንደሚችል የሚብራራበት ነው።
 
የሆነ ሆኖ ተያያዥነት እንዲኖረውም ከሶስት ቀን በፊት፤ እንዲሁም
ከስድስት ቀን በፊት የነበረውንም ሊንክ አክላለሁኝ።
 
የገረመኝ ግን የተወሰነ አትኩሮቱ አቅጣጫው በምክክር ኮሚሽኑ ላይ መሆኑ፤
ጠቅላይ ሚር አብይ ደግሞ በመሃል በቃለ ምልልስ ብቅ ብለዋል።
ለአንድ ወር #መጠሞን#መጨመት እንደምን ፈቃድ ለአጤ
#አትኩሮት ሊሰጥ አልቻለም።
 
ያው እንደ ተለመደው አንዱ አመክንዮ ሳይቋጭ ደግሞ ወደ ሌላው የመንፈስ #ብክነት ……
በዚህ መሃል ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ብቅ ብሎ እንዲህም እንዲያም
ያው ያስኮናል።
 
#የተሰባሰበ#የተማከለ የመንፈስ አቅም፤ የአትኩሮት አቅም በራሱ የውስጥ #ሰላም
ይሻል። ግን ………?
 
የሆነ ሆኖ የአገር ጉዳይ #የትንፋሽ ነውና ማን ይከውነው ማን፤ ይህን መሰል
ግዙፍ አገራዊ ጉባኤ በአትኩሮት መከታተል የተገባ ይመስለኛል።
አገሬን ያለ፤ በዕቴን ያለ፤ መከፋቷን ውስጡ ያደረገ፤ በተለይ በፖለቲካዊ
ጉዳዮች ላይ አትኩሮት ያለው ሰብዕና ስለእናቱ ጉዳይ መከታተል ይገባዋል።
ምን ይሁን ምን? #መሞገትም የሚቻለው በስማ በለው ሳይሆን አክብሮ
ማዳመጥ ሲቻል ነው። 
 
"በየጊዜው እግዚአብሄርን አመስግነው፤
ጎዳናህ የቀና ይሆን ዘንድ ወደ እርሱ
ለምን፤ በጎዳናህ እና በሥራህም ሁሉ
ይከናወንልሃል። በጎውን ምክር ሁሉ
የሚሰጥ እግዚአብሄር ነው።"
(መጽሐፈ ጦቢት ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፱።)
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
 
ሥርጉተ©ሥላሴ።
Sergute©Selassie.
31/07 026.
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።


አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።