#መድህን።
#ምዕራፍ ፲፱።
#ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ወንዞችን፤ ተራሮችን መለያ፤ መወሰኛ አድርገው
አቨው እና እመው ወደ ሠሩልን አቅጣጫ ብንመለስ ዛሬ እንዲህ ህሊናችን
እምስምስ ከሚልበት ትርምስ ወጥቶ ዘመን ሰጥ ሥልጣኔወች ጋር ማተኮር
በተቻለ።
"#የድሮ ናፋቂ " ይባላል ሰላምን መኖርን የሚለግሥ ከሆነ ስለምን አይናፈቅም።
#አንድ ዶላር እና አንድ የኢትዮጵያ ብር እኩል የሆነበት ዘመን፤ በግ ተገዝቶ ቆዳው ተሽጦ ሥጋው ነፃ የሆነበት ዘመን ስለምን አይናፍቅም?
#ለትምህርት ወደ ውጪ የተላከው ሁሉ ስደትን አሻም ብሎ ወደ አገሩ የሚመለስበት ዘመን ስለምን አይናፍቅም?
#አንድ ኩንታል ጤፍ በጥቂት የብር ኖቶች ይገዛ የነበረበት ዘመን ስለምን አይናፍቅም?
#ሰው መሆን ብቻ ቁምነገር የሆነበት ዘመን ስለምን አይናፍቅም?
#የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ከክብሩ ወርዶ የማይነድበት ዘመን ስለምን አይናፍቅም?
#ዜጋ በባዕቱ የማይሳደድበት፤ ሥልጣኔው የማይነቀፍበት ወይንም የማይነቀልበት ዘመን ስለምን አይናፍቅም?
ወዘተ ……… ወዘተ ……… ………ወዘተ ………
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን፤ አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን፤ አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ።
Sergute©Selassie.
31.07.026.
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ