ልጥፎች

ከጁን, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ርትህ ክፍል ሁለት።

ምስል
ርትህ። ክፍል ሁለት። ከሥርጉተ © ሥላሴ 30.06.2018         (ከመንኩሲያዋ ሲዊዘርላንድ።) „ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብጹዕን ናቸው“  (የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፮) ·       እ ፍታ እንዴት አላችሁልኝ የአገሬ ልጆች? ደህና ናችሁ ወይ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። ዛሬ በርካታ ነገሮች ቢኖሩም ቅድሚያ ሰጥቼ ምልከታዬን ላጋራችሁ የምሻው የአፋሩም የሠመራ ጉባኤ ጥያቄ እና የመልሱን ዕድምታ ነው። እርግጥ ነው ይሄ መቅድም ስለሆነ ተያያዥ ነገሮች ማንሳቱ ግድ ይለኛል። የክልሎች ማሰረጊያም ጉባኤ ስለሆነ። ምክንያቱም የጠ/ ሚር አሜኑ አብይ የመንፈስ ነፍስ እኔን እንደ ገባኝ በሁለመና የተቃኘ ንድፍ አለው። የሠመራው ከክልል አንፃር ማጠቃለያው ነው። ቀጣዩ የተጎዱ የቀደሙ የክ/ አገር ከተሞችን እና በአቻነት የሚታዩት ላይ ቢሆን የሚል እሳቤ አለኝ። ቢሆን ምርጫዬ ነው እንደ ማለት።  ደሴ፤ ጅማ፤ አሰላ፤ መቱ፤ ድሬድዋ፤ ሻሸመኔ፤ ሙያሌ፤ ነቀምት፤ ማርቆስ፤ ደብረታቦር፤ አርባምንጭ፤ ደብረብርሃን እንደዚህ በዓመቱ መርሃ ግብር ቢካተቱ መልካም ነው።  አሁን ደሴዎች ሰሞኑን ከአቶ ገዱ አንዳራጋቸው ጋር ውይይት ነበራቸው፤ ተዜትኛው ምዕተ ዓመት እንዳለች ደሴ ግራ ያጋባል። አሁንም ሜዳ ላይ ነው ጉባኤው የተካሄደው። ይሰቀጥጣል። ·       ክ ብረቶቼ። ክፍል አንድ ላይ ጠ/ ሚር አብይ አህመድ „የዙረት አበዙ“ መንፈስ አባዜም አፋር ላይም ተደምጧል። በክፍል አንድ  የጉዞውን ዓላማው አቅጣጫ በሥርጉተ ግንዛቤ አቅርቤያለሁኝ። ቀጣዩ ደግሞ ምምን እንኳን የኤርትራ እና የደቡብ ሱዳን ገና የቀረ ነገር ቢኖርበትም። የእነሱም ቢሆን ሰሞናቱን ባለ ቅኔው ጠ/ ሚር አሜኑ አብይ

ርትህ ክፍል አንድ።

ምስል
ርትህ። ክፍል አንድ። ከሥርጉተ  ©   ሥላሴ 30.06.2018 (ከመንኩሲያዋ ሲዊዘርላንድ።) „በብርሃን ሲያበሩ ሲያመስግኑም ጻድቃን በድንቁርና ከዲያቢሎስ    የተወለዱ ኃጣዕንን በገኃነም ሲወድቁ ያዮዋቸዋል ኃጣዕንም        ጻድቃንን በመንግሥት ሰማያት ሲያበሩ ያይዋቸዋል።“            (መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ ፵፪  ቁጥር ፲፭ ) ·       እ ፍታ! እንዴት አላችሁልኝ የአገሬ ልጆች? ደህና ናችሁ ወይ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ዛሬ በርካታ ነገሮች ቢኖሩም ቅድሚያ ሰጥቼ ምልከታዬን ላጋራችሁ የምሻው የአፋሩም የሠመራ ጉባኤ ጥያቄ እና የመልሱን ዕድምታ ነው። እርግጥ ነው ይሄ መቅድም ስለሆነ ተያያዥ ነገሮች ማንሳቱ ግድ ይለኛል። የክልሎች ማሰረጊያም ጉባኤ ስለሆነ አፋር። ምክንያቱም የጠ/ ሚር አብይ የመንፈስ ነፍስ እኔን እንደ ገባኝ በሁለመና የተቃኘ ንድፍ አለው። የሠመራው ከክልል አንፃር ማጠቃለያው ነው። ስለዚህ በውል ሊፈተሽ ይገባዋል። በምልሰትም አንዳንድ ነገሮችን በብዕረ ብራና ቅኝት ... ቀጣዩ የተጎዱ የቀደሙ የክ/ አገር ከተሞችን እና በአቻነት የሚታዩት ላይ ቢሆን የሚል እሳቤ አለኝ። ቢሆን ምርጫዬ ነው እንደ ማለት። ደሴ፤ ጅማ፤ አሰላ፤ መቱ፤ ድሬድዋ፤ ሻሸመኔ፤ ሙያሌ፤ ነቀምት፤ ማርቆስ፤ ደብረታቦር፤ አርባምንጭ፤ ደብረብርሃን እንደዚህ በዓመቱ መርሃ ግብር ቢካተቱ መልካም ነው። አሁን ደሴ ሰሞኑን አቶ ገዱ አንዳራጋቸው ጋር ውይይት ነበራቸው፤ ተዜትኛው ምዕተ ዓመት እንዳለች ደሴ ግራ ያጋባል። አሁንም ሜዳ ላይ ነው ጉባኤው የተካሄደው። ይሰቀጥጣል። ·       ጣዝማ። „ዙረት አበዙ“ እዬተባሉ የተወቀሱት ጠ/ ሚር አሜኑ አብይ አህመድ አፋሮችም በዚህው አሉታዊ ማዕቀፍ የነበሩ መ

መቼ ልምጣ እና ልይሽ?

ምስል
መቼ ልምጣ እና ልይሽ?          *** ከሥርጉተ  ©  ሥላሴ 30.06.2018 (ከኮሽ አይሏ እናት ሲዊዝ።) „የከበረውን ስሜን የወደዱትን ሰዎችንም በበራ       ብርሃን ከገሃነም አወታቸዋለሁ።“    (መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ ፵፪ ቁጥር ፲፫) መቼ ልምጣ እና ልይሽ ? ዕንባዬን እንድታብሽ፣ አካሌን እንድትዳስሽ በእምነቱ እንድትደባብሽ።                      ናፍቆኛል እና እጅሽ                     የጎረስኩበት ማዕድሽ                     የአደኩበት ጓዳሽ                     የፏለልኩበት ሜዳሽ                     የዘለልኩበት መስክሽ                     የሮጥኩበት ዓውድሽ። መቼ ልምጣ እና ልይሽ? ዕንባዬን እንድታብሽ አካሌን እንድትዳስሽ፣ በእምነቱ እንድትደባብሽ።                      የሳቅኩበት አድባርሽ                      የአሥራ ሦስት ወራት ብርሃንሽ፣                      ሀሁ ... ያልኩበት ገበታሽ                      የዕውቀት ሸማ ሻሽ-ሽሽ፣                      የቤተዘመዱ ውሎሽ                      የአንችነትሽን - አዋ ዋ ልሽ። መቼ ልምጣ እና ልይሽ? ዕንባዬን እንድታብሽ አካሌን እንድትዳስሽ በእምነቱ እንድትደባብሽ።                       ተፈጠሮዊው ልማድሽ                       የፍቅር ጎለጎታሽ፣                       የወግ - የትውፊት፣ ህግሽ                       አስርቱ ቃላት መንበርሽ