ልጥፎች

ከጁላይ 7, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

እቴጌ ጣይቱ ቶማስ።

ምስል
እቴጌ ጣይቱ ቶማስ። ከሥርጉተ  ©   ሥላሴ  (07.07.2018።) (ከደጊቱ ሲዊዝሻ።) „ለሁሉ ጊዜ አለው ከሰማይ በታችም   ለሆነው ነገር ሁሉ ጊዜ አለው።“ (መክብብ ምዕራፍ 3 1) መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=f7N2xbsODz8 https://www.youtube.com/watch?v=NdTDI2xfS3U ኢትዮጵያዊነትን ፍለጋ - ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ለአመታት የተደረገዉ ጉዞ የተወለደችው በታላቋ ብርቴን ነው። ከዛ ወደ ጃምይካ ከዛም ኑሮ በአሜረካ። አያቷ ጎጃሜ ናቸው። ለተወሰነ ዓመት ባህርዳር ቆይታለች። አሁን ግን አዲስ አበባ ነው የምትኖረው። አዲሱ የ ዓለምን ሚዲያ እያስደመመ የሚገኘው የሞድ ኢንደስተሪ ባለሙያ ናት። የሠለጠነቸውም አውሮፓ ውስጥ እንደሆነ ከቃለ ምልልሷ ለማወቅ ችያለሁኝ። ዕንባ ፍል ነው? ግን ስለምን ፍል ሆነ? ዕንባዋን ማቆም አልተቻላትም። ሐሤቷ ወደር የለውም። ኢትዮጵያዊ ዜግነት በማግኘቷ። የኔዎቹ ዛሬ ስለ ድንቅነሽ ድንቂት ትንሽ ላወጋችሁ ፈለግሁኝ። „ኢትዮጵያ እምነቴ ናት“ ትላለች። ኢትዮጵያዊቷ እቴጌ ጣይቱ ቶማስ ለእኔ የኢትዮጵያ ጥበብ ናት። ሥነ - ህይወት ናት። ሥነ - ሥህን ናት። ሥህነ -መሆን ናት። ሥህነ - ነፍስ ናት። የእኔ ጣይቱ የልቤ መስረቲቱ የመሆን የኔይታይቱ። የእኛዊነት አርበኛይቱ እቴጌ ጣይቱ ቶማስ ውቢቱ። ድፍን ጠይም ፎለቄዩቱ የኢትጵዮጵያዊነት ሰንደቂቱ እጬጌይቱ! የትናንቷ አንሻ የድንቅ ነሽ ድንቂቱ የመሆን ብሥራት ጣይቱ የድል ዜና ህብሪቱ የኛይቱ ጣይቱ። የትውፊት እቴጌ ቀለሚቱ የብጡል ፍቅር ሰብሊቱ። አንቺ ጣይቱ የመውደድ አብነቲቱ!!

እርድ በሰማያዊ ተቀይ ጋር … በበረደው የጨዋታ ትዕይንት፤

ምስል
ታጠፊያ አልጋ ይዞ ሜዳ የገባው የሲወዲን  ቡድን ለሽ እንዳለ እንግሊዞች  ለቀጣዩ ጨዋታ አለፉ።  „ለሁሉም ዘመን አለው፣ ከሰማይ በታችም ለሆነው ነገር ሁሉ ጊዜ አለው።“ (መክብብ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፩ ) ከሥርጉተ ሥላሴ 07.07.2018 (ከደጓ ሲዊዝ።) ·        ከእረ ፍ በፊት ስለነበረው ጨዋታ። ዛሬ ፈታ ያለ ቀን ነው። ገብያውም ደርቷል። ርገጡኝ ላለ ለፈቀደ ምን አለ። የትናቱ አልጠቀመኝም ዛሬንም አለሁላችሁ ኑልኝ የተባባራችሁት እግሮች ሆይ ብላ ድንቡልቡሊት ይሄው ትደሰቃለች። እንግሊዞች ተ30 ደቂቃው ላይ ገድ ሰጣቸው እና አንድ ለምንም በሆነ ውጤት የመጀመሪያውን ጨዋታ በግል አጨዋወት ዘይቤ የበላይነት በተጫነ የማጥቃት አቅም ጢባ ጢቦ አጨውተውቸዋል ሲዊዲኖችን በተወሰነ ደረጃ ለጥቂት ደቂቃ ቢሆንም።  በቡድን ጨዋታ ቢቀምሩት ኖሮ ያገኟቸውን ወርቅ ዕድል ቢጠቀሙበት ሁለት መረብ እንኳን ደህና መጣሽ በሚል ማከያ ሦስቷን ጨበጥ አድርገው እረፍታቸውን ያጣጥሙ ነበር። እኔ ለእንግሊዝ ቡድን የገጠማቸው ቡድን ስውዲን ስለሆነ ከዚህ የበለጠ ነጥብ ማምጣት ይጠበቅባቸው ነበር። በማሃል ሰፊ ክፍተት ነበረው የእንግሊዝ ቡድን። አንድ ሰው ብቻ ሳይሆን ቲም ወርክ ያስፍለጋቸዋል። በእኔ ግምት የገጠማቸውን ዕድል በመጠቀም እረገድ ያደረጉት ጥረት ዝቅተኛ ነው። እኩል የመሮጥ እኩል መፍጠን ይጠብቃባቸዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካም እንዲሁ ነው ኦህዴድ ኳሷን ይዞ ወደፊት ይገሰግሳል፤ አባል ድርጅቶች ግን ባሉበት ይድሃሉ፤ ተፎካካሪዎች ደግሞ  የዘጋቢነቱን ደርሻ ይዘውታል። ያዬሁት ድክመት የፍላጎት የኮኦርድኔሽ ስስነትን ነው። የእንግሊዝ 10 ቁጥሩ የሚጥረውን ያህል ሌሎቹ አልነበሩ ማለት ያስ

ሬሳ ሃሳብን ለተስፋ ማለም መሬሳነት ነው!

ምስል
አማራጭነት በሌለ እውነት ተስፋን ተጠራ ማለት ያማል። „እግዚአብሄር በዬሥራቸው ፀንተው የሚኖሩትን      ሁሉም አውቀው በህጉ ይጠብቃሉ።“ (መቃብያ ቀዳማዊ ምዕራፍ 21 ቊጥር 20)    ከሥርጉተ ©ሥላሴ (07/07/2018)     (ከኮሽ አይሏ ሲዊዝ።) ·        መነሻ። https://www.satenaw.com/amharic/archives/60177 „የኢትዮጵያ ፖለቲካ የለውጥ ጉዞ ከትናንት ዛሬ ቢሻልም ነገ ላይ ጥርጣሬ አለን  (ስዩም ተሾመ)“ ·        ጠብታ። ዛሬ ፏ ብላለች ልዕልተይ። ስለሆነም በጥዋቱ ቁርስ ሳልበላ ነው መጣፍ የጀመርኩት። ያስነሳኝም አልጋዬ አጠገብ ባስቀመጥኩት ማስታወሻዬ ላይ ተጋድሜ የጠፍኩትን ሥነ ግጥም ጡሁፍ መለጠፍ አስኝቶኝ። ተዚያ በሆዋላ ሳተናውን እንዴት አደርክ ልል ስገባ እንድ ሁለት ጹሑፎችን አገኘሁኝ። ተነበቡ እናም ዕይታዬ ተጣፈ  እንዲህ … ·        እንዲህ በዛሬው ጡሁፍ አንድ ልባም ነገር ሳነብ „ወያኔ ሃርነት ትግራይ“ ከግንባሩ ከወጣ ብቻ እና ብቻ ነው የመፍትሄ መንገዱ ይላል። እስከ አባላቶቹ እና ደጋፊዎቹ ድረስ ራሱን ችሎ ከኢህአዴግ ግንባር ወጥቶ እንደ አንድ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ኢትዮጵያ መሬቷን ያቆዮዋት የቀደምት አርበኞቻችን የነዘረይ ደረስም ስለሆነች እኩል እንደ ማንኛው ዜጋ መወዳድር እንዲችል ከተደረገ ያ አንድ መንገድ ነው። ዜግነትን ነሽም ሰጪም የለም እና። ይሄ የሚደገፍ ነው። ወጥ ፓርቲ የመሆንን ሃሳብ ሠመራ ላይ ባለው ጉባኤ ስለተነሳ ግንባሩ ሊከብደው እንደሚችል ጽፌ ነበር። እርግጥ ነው በጥናት ላይ የተደገፈ እንደሚሆን ቢገለጽም በሌላ በኩል በመደመሩ ፓለቲካ ያሉ ሌሎች ንጥረ ነገሮችን ቢታከሉበትም በ

የሚለምኑትን ሰዎች ልመናቸውን ይሰማቸዋል፤

ምስል
„የሚለምኑትን ሰዎች ልመናቸውን ይሰማቸዋል፤ በንፅህና የልቡና ፈቃዱን የሚያደርግን ሰው ልመናውን ይቀበለዋል። እሱም ጸሎታቸውን ይሰማቸዋል፣  በለመኑትም ሁሉ ፈቃዳቸውን ያደርግላቸዋል። (መቃብያን ቀዳማዊ 21 27) ከሥርጉተ ©ሥላሴ 07.07.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።) መሸታ የሸመነ መሸተኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛኛ ካልገለበጠ የማያስተኛ።                    ማገዶ ተከፍሎ ለመናኛ                         የሥም አያሌው መጋኛ።                            በመሾር ሽሮ ግርፋቱ                               የመግል መቅኖ ለመብላቱ።                                  የጪስ ተወይራ ተገድግዶ                                       ፍሙን ማን ደፈርት ተሸልቶ።                                            አያልቅም ፊደል መከረኛ                                               የዙር ተመለስ ዛሬኛ።                                                  የቄራ ጥቅጥቅ ሸር ጠጥቶ በመዋል                                                            ያፍ ሰብል ምርቱ ሲዋልል።                                                                   መዋል አልዋለም ከነክቱ                                                                       የትነበር የኩራት አልባሳቱ?