የአማራ ትግል የህልውና ከተባለ ለምን "መግደል፤ መጨከን፤ ማስጋት፤ #ዛቻ አጀንዳ ሊሆን ቻለ?
የአማራ ትግል የህልውና ከተባለ ለምን "መግደል፤ መጨከን፤ ማስጋት፤ #ዛቻ አጀንዳ ሊሆን ቻለ? የሰው ልጅ ሰርክ ሞቱ ከሆነ እንደ እህል #ያልቃል ? #መገደልን ለማስቆም አነጣጥሮ #መግደል መፍትሄ አይሆንም። ማስጨነቅን ለማስቆም ጫናዊ ማስጨነቅ ጎዳና ሊሆን አይችልም። መሳደድን ሃራም ለማለት #ዛቻ ስጦታ ሊሆን አይገባም። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፰። እኔ የአማራን ትግል በሁለት ከፍዬ አየዋለሁኝ። 1) የማንነት ትግል። 2) የህልውና ትግል ብዬ። ይህን የምልበትን አመክንዮ ፌስቡክም ሳልጀምር፤ ከ፲፪ ዓመታት በላይ ብዙ ጊዜ በዝርዝር ስለፃፍኩበት ደክሞኛል። የአሁኑ ዝምታዬም ማህበራዊ መሠረቱ የተናደበት ሁሉ ወደ ዘርፋ #ስለተመመ በጥሞና ማድመጡ ይበቃል ብዬ ስለወሰንኩኝ ነው። "በሉት! በርቱ! አሳዱት! ግረፋት!" የሚላችሁ የሚዲያ ባለቤት ሁሉ ሙሉ ሦስት ዓመታት የተፈጠሩበት የደቡብ ቀጠና፤ ለብልጽግና ቀጥ ለጥ ሰጥ ብሎ እየተገዛ መኖሩን አስከብሮ ይገኛል። ደቡብ ጫካ ጠፍቶ ነውን አንድ የፋኖ ሻለቃ ማደራጀት ያቃተው? ዛሬ በብልፄው ካቢኔ ውስጥ 50+ ደቡብ ነው። በዘመነ ህወሃትም እንዲሁ። ድል ቢቃረብ እዛው ሚዲያቸው ላይ እንደተለመደው የእንቶኔ የነፃነት ፋኖ ተብሎ ተደራጅቶ የድል አጥቢያነቱን ሲታወጅ እናዳምጣለን። አሁን ግን ሰርክ ሞት፤ መከራ፤ ጭንቅ፤ ፍርሃት በገፍ ይቀናለታል ለአማራ "ጀግና" በሚል ቅጥያ። እነሱ ህዝባቸው #ማገዶ እንዲሆን ፈጽሞ አይፈቅዱም። ፡ተቋሞቻቸው ደርጅተው ሙሉ አገልግሎት እንዲሰጡ፤ ተጨማሪም አዳዲስ ፕሮጀክቶች ተወጥነው ከግብ እንዲደርሱ ነው የሚጥሩት። በብልፄው መዋቅርም ከውጭ ጉዳይ ...