ልጥፎች

ከሜይ 7, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ዐይንም ጠንካራ መልዕክት ይልካል።

ምስል
ዐይን ቋንቋ አለው። ዐይንም  ጠንካራ መልዕክት ይልካል።  ከሥርጉተ - ሥላሴ ( Sergute © Sselassie )  02.04.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)  „እግዚአብሄርን አንዲት ነገር ለመንሁት፤ እርስዋንም እሻለሁኝ፤  በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሄር ቤት እኖር ዘንድ፤  እግዚአብሄርን ደስ የሚያሰኘውን አይ ዘንድ፤  መቅደሱንም እምለከት ዘንድ“   (ከልብ አምላክ መዝሙር ፳፮ ቁጥር ፬) ·          እ ፍታ። ትንሽ ነገር ማለት ፈለግሁኝ። ቋንቋ የፍቅራዊነት (LoveIsm) ረቂቅ ሚስጢር ነው። ቋንቋ የራሱ ሥርዓተ - ህግጋት አሉት። ቃል በሥርዓቱ ውስጥ ሲተገበር ሥርዓቱን ተከትሎ ቤተሰብ ይመሰርታል። የመጀመሪያ የቋንቋ ቤተሰቡ አረፍት ነገር ነው። አረፍተ ነገር ደግሞ ከፍ ያለውን ዞጉን ሲፈጥር ሐረግን ይመሠርታል። ሐረግ ሙሉ ገጽ ሲኖረው ልክ እንደ ፍጡራን ሐገር ይሆናል ቋንቋ - ለእኔ። እንሰሳት ቋንቋቸውን የሚገልጹት ወጥ በሆነ ድምጽ ነው፤ በነገራችን ላይ የእንሰሳት ድምጽ በስዋሰው የተቀመረ አይሁን እንጂ ከሰብም በላይ ግሎባል ነው። ደንበጫ ያለው ዶሮ ኒዮርክ አካባቢ ካለው ገጠር ከሚኖረው ዶሮ ጩኽቱ ጋር ተመሳሳይ እና ወጥ ነው። ጋና ያለው ውሻ ሲዊዘርላንድ ካለው ጋር ተመሳሳይ ድምጽ ነው ያለው። አውስትራልያ ላይ ያለው በግ ይሁን ፈረስ፤ ፈረስ ይሁን ወይፈን ብራዚል ውስጥ ካለው ጋር ተመሳሳይ የድምጽ አገላለጥ አለው። እንሰሳትም እንደ ሰው አካላዊ ቋንቋ አላቸው ብዬ አምናለሁ። ፍቅርን ሲፈልጉ፤ ቁልምጫ ሲፈልጉ፤ አትኩሮት ሲፈልጉ፤ ታማኝነታቸውን ሲገልጹ፤ ሲበሳጩ፤ ጸጥታን ሲፈልጉ በአካላዊ ቋንቋ መልእክት ይልካሉ።  ወደ ቀደመው ስመለስ ከሰብ የቃል አንደበታዊ ልሳን ጋር የአካላት ቋንቋም አለ።

ኢትዮጵያን ቁምነገር የማድረግ ዓላማ!

ምስል
ኢትዮጵያን ቁምነገር የማድረግ  ዓላማ  በመሆን ውስጥ ይታያል። ሥርጉተ - ሥላሴ  ( Sergute © Sselassie ) 31.03.2018 (ከጭምቷ ሲዊዚርላንድ።)                                    „እግዚአብሄር የርስቴ እድል ፈንታና ጽዋዬ ነው።“ (መዝሙር ፲፭ ቁጥር ፭) እፍታ።   አዎን ይታያል። „አዎንታዊነት መሆን“ በልቡ ውስጥ ለተጻፈ ኢትዮጵያን ቁምነገር የማድረግ ዓላማ አለው። ይህም ማለት „አዎንታዊነት የመሆን ህግ“ በልቡ ለተጻፈ ኢትዮጵያን ቁምነገር የማድረግ ዓላማ ያለው ብቻ ነው። „አዎንታዊነት በመሆን“ ውስጥ መኖር አለ። በመኖር ውስጥም „መሆን“ አለ። በመኖር ውስጥ ያለው „መሆን“ ራሱን „መኖርን“ ለማኖር የተፈጠረ መሆኑን ያውቃል። አንድ ሙሉዑ ሰብዕና ማለቴ የሞራል ስብራት የሌለበት „አዎንታዊ መሆንን“ ለማኖር በቅድሚያ „በአዎንታዊ መሆን“ ረቂቅ ምግባራዊ ስበት ውስጥ በዘላቂ ለመኖር ቁርጥ ውሳኔ ማድረግ ይጠበቅበታል። „መሆንን“ „መሆን“ የሚያደርገው „መሆን“ በዕውን „መሆንን“ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥርዓቶችን መከተል ሲቻል ብቻ ነው። እያንዳንዱ የመኖር ክስተተ - ነገር የዬራሱ ሞራላዊ ወይንም ኢ- ሞራላዊ ሥርዓት አለው። ሞራላዊ ሥርዓት በራሱ የሚለግሰው ቁምነገር ዓላማን ለማሰካት በክስተቱ ውስጥ ሥርዓተ አልበኝነት ወይንም ኢ- ሞራላዊነት እንዳይከሰት የሚያደርግ ጥንቁቅ ወታደሩ ነው። እርግጥ የተጻፈም// ያልተጻፈም፤ ሃይማኖታዊ // መንግሥታዊ ወጋዊ ወይንም ልማዳዊ፤ ወይንም ባህላዊ ሊሆን ይችላል። አንዱ  በአንዱ ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ እንዳይሆን ወይንም አንዱ በሌላው ላይ የክስተቱ ተፈጥሮ ጨቋኝ እንዳይሆን እንደ አፈጣጠሩ እንያንዳንዱ ክስተት በሁሉም የህግጋት ሂደቶች በው

ግብዕቱ አይቀሬ!

ምስል
የበረከት የሸር ሸጎሬ፤ ግብዕቱ አይቀሬ! ከሥርጉተ - ሥላሴ 14.03.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) „ፍርድ የቅዱሳን ቃል ነው።“ (ትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፰።) ·          ሰ ው በሀገሩ ተሰዶ በስደትም ተሰዶ።  የስደቱ ዘመን 27 ዓመት ሆነው። ስደቱ የቁስ ቢሆን ምን ያህል ሚዛኑ ይቀል ነበር። ስደቱ የመንፈስም ጭምር ነው። ስደቱ የአዕምሮም ጭምር ነው። ይህ „ነፃነት“ የሚባለው ቅብዕ ቅዱስ በሀገሩ፤ በመሬቱ፤ በቀዬው ተሰቃይቶ ተሰዶ ነው የኖረው። ለዚህም ነው ዝልቦ ሃሳብ ተሸካሚው „ኢህአዴግ ባህሉን መልቀቅ የለበትም“ የሚለው የአቶ በረከት ሴራ ልቅልቅ ቅዠት። የአቶ በረከት የሸር ሸጎሬ ግብዕቱ ግን አይቀሬ ነው። አይችለውም ይህን የኦህዴድን „ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው“ ገድለ ታምር። ·          የወ ል አዱኛ  እና ፈተናው። ኢትዮጵውያን የወል አዱኛችን የምንለው በቅኝ አለመገዛታችን የሰጠን የሥነ - ልቦና ልዩ የመንፈስ መቅኖ ነው። ይሄን የዘመናት ገድለ - ታሪክን የአቶ በረከት ስብዕና የመሸከም አቅሙ ራሱ ዝልብ  ነው። ለኢትዮጵውያን ግን በነፃነት መኖር የሰጠን ረቂቅ መንፈሳዊ ሲሳይ ስላለ ቀን ቢበራከትም እውን መሆኑ ግን አይቀሬ ነው። ይህ መንፈስ የትኛውም መዝገበ ቃላት አይተረጉመውም። ከእኛም አልፎ ተርፎ አፍሪካን በሥነ - ልቦና ሙላት አይዟችሁን የቀለበ የማይነጥፍ ጥገት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ጥቁር ህዝብ ነፃነትን በመዳፉ መሥራቱን ዓለምን አስተምሯል። ሐዋርያ ነው፤ ሰባኪ ነው ኢትዮጵያዊነት። ኢትዮጵያዊነት አፍሪካዊንት ብቻ ሳይሆን ብሄራዊነትም ነው። ተፈርያንን ማሰብ ልባምነት ነው። ገድሉ የጥቁር ህዝብ የማድረግን፤ የሥነ - ልቦና ሥልጣኔም ምንጩ ይሄ የተጋድሎ የመስዋዕትነት ዓርማ ነው። ይህ ትርጓ

ፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ ምህዳን ነውን ...?

ምስል
ፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ ምህዳን ነውን የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስቴር ቅብዕ የሚሰጠው? እንዴት ተቀለደ? እንዴትስ ተደፈርን?! ንቀቱ ደንበር የለውም! ከሥርጉተ ሥላሴ 01.03.2018 (ከጭምቷ - ሲዊዘርላንድ) „ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች“   (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 67 ቁጥር 31) ·          በር። ከኤርትራ የሚነሳ ወጀብ ሁልጊዜም መንፈሳችን ከፋፍሎ፤ አቅማችን ተርትሮ ሲያዋጋን ኑሯል። አገር ብለዋል፤ ሆነዋል። ምን ይፈልጋሉ? ስለምን ከኢትዮጵያ እራስ መውረድ እንደማይፈቅዱት ሚስጢሩ አንድ ነው። አቅም ያላት ኢትዮጵያን ከመፍራት የመነጨ ነው። ትናንት የተፈጠረችው ኤርትራ ዛሬ ከ3 ሺህ ዘመን በላይ የታሪክ አውራ የሆነችውን የኢትዮጵያን ቅዱስ መንፈስ ለመምራት፤ አንበርክካም ለመግዛት ትሻለች። አለማፈር። ልክንም አለማወቅ። ለነገሩ ኤርትራ በምታሰናዳው አጀንዳ እኮ ነው ሁለመናችን ስንገብር የኖረንው። አቅማችን ለቁርሾ ስንቅ ስናጭ፤ ስንድር የኖርነው። በሃሳብ ገብታ ውጊያ ስንት አቅም ጊዜ እና መዋለ ንዋይ ፈሷል።  „ሁሉም የኢህአዴግ ምክርቤት አባላት ለግንባሩ ሊቀመንበርነት መወዳደር እንደሚችሉ ዘረኛው በረከት ስምኦን ገለፀ“ http://www.satenaw.com/amharic/archives/51852 ·          ኢትዮጵያን ሞታ የማዬት ናፍቆተኛው የፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂ የመንፈስ ርግጫ። „ለራሷ ሲያርባት የሰው ታማስላለች።“ የማረተ ቆርቆሮ ተሸክሞ ዕድሜህ ይፍታህ በተባለለት በኤርትራ ህዝብ ላይ የበዬደው የፕ/ኢሳያስ አፈወርቂ ካቢኒያዊ መንፈስ የወያኔ ሃርነት ትግራይን አዝሎ እና ከብክቦ ለዚህ ሁሉ መከራ እናት ሐገር ኢትዮጵያን መዳረጉ አልበቃ ብሎ፤ ዛሬም በሰላዩ የቁርጥ