የአንቡላ ቃርምያ!

የአንቡላ ቃርምያ!
ከሥርጉተ ሥላሴ(Sergute©Sselassie)
 26.02.2018 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)
„ሳትናገር አስቀድምህ ነገሩን ተረዳ። በሃጢያት ሳትታመም ንሰሃ ግባ።“ 
(መጸሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፲፰)

ጤና ይስጥልን ብለናል እኔ እና እመቤት ብዕሬ ለጎንደር ባለጣውንት አቦይ በረከት ስምዖን።
 ግን እንዴት ነው ትንሽ አሰርውሃ ነገር ጠፋ መሰል? ከቶ የሴራው ቸረቸራ በሽሁራር ተዋጠ ይሆን?
·         ወደ መነሻ ይገስገስ … http://www.satenaw.com/amharic/%E1%8B%A8%E1%89%A0%E1%88%A8%E1%8A%A8%E1%89%B5 „የበረከት ስምኦን  ለቅሶና ተቃውሞ  በዶ/ አብይ አህመድ  እና በኦብኤን ቲቪ ላይ“
·         እንዲህም ሆነ …
በመጋቢት 24.2015 አንድርያስ ሉቢስ (Andreas Lubitz) የሚባል የጀርመን ዊንግ ረዳት አውሮፕላን ወጣት አብራሪ አቅዶ እራሱን ጨምሮ ወደ 149 ሰው ከተራራ ጋር አጋጭቶ አሰቃቂ እልቂት ፈጸመ። ሰቆቃው እጅግ አስከፊ ነበር። እሬሳው ከተለቀመ በኋዋላ ታች ላሉት ኤሊኮፍተር ይመጣላቸዋል፤ ገመድ ሲላክላቸው ሬሳውን እንደታቀፉ በኤልኮፍተር ተንጠልጥለው በብዙ ገመድ ታስረው ሬሳ ተሽከመው አዬር ላይ በወጀብ እዬተናጡ ነበር የሚጓጓዙት። ያን ጊዜ እንቅልፍ አልነበረኝም፤ እህል ውሃም ትንፋሽ ለማሳደር ያህል ነበር። ታስተውሱ ከሆነ የካቲት ላይ ደግሞ የእኔ ጀግና ረዳት አውሮፕላን አብራሪ ሐይለመድህን አበራ ያ ብርቱና ሃላፊነት የሚሰማው ጠንቃቃ፤ ብልህ ወጣት ሰውንም ንብረትንም ካተረፈበት የተቀደሰ ቅኑ ዕለት ብዙም ሳይርቅ ነበር። ከዛ በኋዋላ ሰማይ ማንጋጠጥ ልማዴ ሆነ። በአውሮፕላን ለሚጓጓዙ ሁሉ ጭንቀታም ሆንኩኝ። ጀግናዬ በሰላም ሲዊዝ ጄኔባ ላይ አርፎ ግን አስከ አሁን ድረስ ሳስበው ይሰቀጥጠኛል። በዚህ በጭንቀት በሰመጥኩበት ማግስት ነበር ይህ ደግሞ የተደረበው። እጅግ አሰቃቂ ነበር። ለሶስት ሳምንት የዘለቀ ዘመቻ ነበር። ሥራው ፈታኝ ነበር። ጀርመን፤ ስፔን እና ፈረንሳይ በጥምረት ነበር ፈተናውን በወል የተወጡት።
·         ተፈጥሮን ስለማሰብ።
ስለምን ይሄ ወጣት እንዲህ ክፉ ነገር አሰበ በማለት አንድርያስ ሉቢስ የህሊናዬ አብይ አጀንዳ ሆነ። ልጆች የህጻናት ማሳዲጊያ ከሚገቡበት ዕለት ጀምሮ በሰው ልጆች ተፈጥሯዊ ፍቅር ላይ ያተኮረ ሥርዐተ ትምህርት ሊማሩ ይገባል ብዬ በግሌ ወሰንኩኝ። ፍቅር ሰውን ያድናል። ግን በተለምዶ ሳይሆን ሙያዊ መሆን አለበት። የሚማሩት፤ የሚመረቁበት፤ ምርምር የሚካሄድበት ወዘተ …
ሃሳቤንም ለሚመለካታቸው ዓለም ዓቅፍ አካላት ላኩኝ። ከዛ በኋዋላ ዓመቱን ሙሉ የስሜት ንክኪ ነገሮች ላይ የተለያዩ ሁኔታዎችን ማጥናቴን ቀጠልኩኝ። „ስሜት“ የሰውነትን ሰራዊት ጄኒራል ነው። ቁጡነት፤ ብስጩነት ወዘተ … በዚህ ዙሪያ ዓለም ምን እዬሰራች ነው? ብዬ ሳስ የተለያዩ መረጃዎችን አገኘሁኝ። በተለይ „ሜዲቴሽን“ በሚመለከት ያለው ውጤት ጥሩ ፍንጪ ነበር። በዚህ ፍንጭ ተጓጉዤ አሜሪካን ሐገር እንደ ገናም ጀርመን ሐገር በዚህ ዙሪያ ብስጩነትን የማስታገሻ መንገዶችን ተከትሎ የተሠሩ ተግባራት እና የተገኙ ውጤቶችን ተከታተልኩኝ። የትውልድ ነገር ስለሚያስጨንቀኝም በመደበኛ የጀርመን፤ የኦስትራሺን እና የሲዊዝን የወጣቶችን የተለያዩ ውድድሮች እከታተላለሁኝ። ዓለም አስፈሪ እዬሆነች ስለመጣች። በጋራ የውድድር ቆይታ የአብሮ መኖር ዕድል ሲገጥማቸው ከቡድኑ ውስጥ የእስያ ደም ያለባቸው፤ ከሌሎች በተለዬ መልኩ አብዛኛውን ጊዜ ልዩ የሆነ ሰብዕና አይባቸዋለሁኝ። ስለምን ይሆን ብዬ ደግሞ ወደ እስያ በስሜት ጎራ ተፈተሽ እስያ ስል፤ የእስያ ልጆች እብዛኞቹ ጤናማ እና የተረጋጋ መንፈስ አላቸው። ምክንያቱ ምን እንደሆነ ስከታተለው ያው ከሜድቴሽን፤ ከዮጋ አደረሰኝ። ፈተንኩት። በራሴ ላይ ሠራሁበት።  
ከዛ ቀጥዬ እማማ አፍሪካስ ምን እየሰራች ይሆን ብዬ ስኳትን ነው የኛውን ድንቅ ዶር ምህረት ደበበን ያገኘኋዋቸው። ያን ቀን ደስታዬ ወደር አልነበረውም። እሳቸውን ሳገኝ የሳቸውን ቃለ መጠይቅ፤ የሠሯቸውን ተግባራት፤ ያቋቋሙትን ፕሮጀክት ስመረምር ነበር የዶር አብይን አህመድን ጉዳይ ያገኘሁት። ይህ መልካም ጅምር በነበረበት ጊዜ ለአቦይ በረከት  ስምዖን ዶር አብይ አህመድ ስጋት አልነበሩም። የሳይስንስና ቴክኖሎጂ ሚር/ በነበሩበት ጊዜ ከእርምጃ ወደ ሩጫ ሞቶ ላይ ስብሰቡ ከድንቅ በላይ ነበር። የስበስቡ አመራረጥ የደረጀ እና ዓላማውን በዘለቄታ ለመሳካት ከጉልቱ የተነሳ ነበር።ቀደምቶችን ፈላስፋዎቻችን ተወት አድርጌ ግን በወጣቶች ላይ የነበረው አትኩሮት ሳበኝተተኪ ትውልድ ማፍራት ለዶር አብይ አህመድ የነፍስ ያህል ነው። ተከታታይነት ብሩህ አጀንዳ ነው። ተንታኞቹ በዬተሰጣቸው እርአስ ጉዳይ  ዶር. ምህረት ደበበ፤ / ጽዮን ተክሉ፤ ዶር ብሩክ ለምቢሶ ሙሉ ዕድሜ ላይ ያሉ፤ አቶ ዮናስ ደስታ  ወዘተ ነበሩ ። ሃሳቡ ከተነሳ አንድ ለአቦይ በረከት ሲለጥቅም / ኢሳያስ አፈወርቂን የሚነስት ወይንም በእንቅጥጠቅጥ የሚሰለቅጥ ክኒን ልግለጥ።

·         እንደ እሸት ቅመሱ፤

 … አቶ ዮናስ ደስታ ካሉት … ከስማርት ፎን ፍልስፍና በፊት ኢትዮጵያ የቀደመችበት አብይ ጉዳይ አለ ይሉናል። „የመጀመሪያው ስልጣኔ ሊሆን የሚችለው የሰው ልጅ ከአካባቢው እራሱን ፊድ ለማድረግ የተጠቀማባቸው ስቶን ቱሎች ናቸው። the most papleshed stone ይሏታል ያቺ ስቶን ቱል ጎና የሚባል ኢትዮጵያ ወደ ደቡብ ላይ ያለ የተገኘች ድንጋይ ስትሆን 2.6 አንድ ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ያላት ናት። ከዛች የድንጋይ መሳሪያ በፊት የተገኜ ቴክኖሎጂ ስሌላ ስማርት ፎን … ወዘተ … መነሻው የእኛ ነው።“  ስለ እጽዋት ፕ/ ሰብስቤ ደምሴ ደግሞ እንዲህ ይላሉ „ብዙ እማናውቃት የህብነት የሚባል በሱማሌ /ኢትዮ/ ክልል  ውስጥ balanced (diet) የሆነ ምግብ ስለመሆኑ ተመስክሮለታል።“  አንደ ሽፈራው ቅጠል ማለት ነው። እና ከእነ ቁጭበሉ ጋር ይህን የሊቃውንት ጉባኤ ያደራጀ፤ የመራ፤ ስለ እናቱ በጥልቀት ሊመራመር የፈቀደ … የእናቱ ቀደምትነት እና ኋላቀርነት አለመመጣጠን ሩሁ አድርጎ ለያዘ ቅን፤ ሩህሩህ፤ አዛኝ፤ ለማወቅ ጉጉት ያደረበት፤ ራሱን ዝቅ ያደረገ ለእናቱ መታመንን የሸለመ መንፈስ ጋር እንዴት ከነአለቅት ጋር … ጋዳ ነው …
·         የትቅማጡ መነሻ በጥቂቱ።
1.       አቦይ በረከት ስምዖን በቀጥታ ሥራ ፈት ይሆናሉ። የብዕር ቅርሻቸው የሽሁራር ማራገፊያ ይመክናል። „የአፍሪካ ነብርነት“ ፉከራ ¡እንዲህና እንዲያ … ቀልድ ስምጥ። 
2.       በኤርትራ መንግሥት የተሰጣቸው ስውር የስለላ ልዩ ተልዕኮ፤ ሃላፊነት እና ግዴታ ወደ መቃብር ይወርዳል።
3.       እንደ ተፈለገ ቢሮ ሆነ ቤት ተገብቶ ካሜራ ገጥሞ፤ ድምጽ መቅጃ ገጣጥሞ መሰለል ያከትማል። ዕውቀቱ ከነሙሉ ቁመናው መዳፍ ላይ ስለሚኖር የስላለ ሰላላን እሞክረዋለሁ ቢል ግጥግጡ መላላጥ ብቻ ነው የሚሆነው።
4.       የስለላው ውጤት ሁለመናዋን ቀጤማ አድርጎ ለጥቃት ማጋለጥ ወዘተ … ግባዕተ መሬት …
5.       ጣልቃ እዬገቡ መንጨቧረቅ ሆነ ወጥ እንጨት መሆን ይቀራል። በተዘዋዋሪም ቢሆን የሚቻል አይሆንም። በፍጹም የታመኑባቸው ጉዳዩች በመርህ እና ለወቅቱ በሚያገለግለው ህግ ብቻ ይከወናል። ከህግ በላይም ከህግ በታችም መወዛወዝ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ ይባላል። ክልሎችን መነሰተም መልክ ይይዛል።
6.       ተጠያቂነት እና ሚዛናዊነት ከዝቅተኛዋ ሐገራዊ ጉዳይ እስከ ከፍተኛው ድረስ ባለቤቱ ውስጥነት ይሆናል። ጥምና፤ ቅልውጥ ይሰናበታል። በሐገር መደራደር … አከርካሪው ወጌሻ አልቦሽ ይሆናል።
7.       ከረባት እያንጠለጠሉ የውሸት ቁጥር መደርደር ያከትማል። ችግሩ በልኩ ይጠናል። የመፍትሄው ዘለቄታ መለኪያው ጭንቅላት ስለሆነ በዛም የሰራበታል።
8.       ትልቅ ሐገራዊ ፕሮጀክት አቅዶ በስብሰባ በዛብኝ ሰበብ ቀልድና ቁም ነገር ግብዕቱ ይፈጸማል። አላግባብ የጊዜ፤ የህሊና፤ የመዋለ ንዋይ፤ የታሪክ ብክነት በአግባቡ ይመራል።
9.       ተዘርፎ በድልቂያ የሚራወጣው የዳንኪራ ዲስኮ ቤቱ ይከረቸማል።
10.   ርህራሄ፤ ሰዋዊነት፤ ተፈጣሯዊነት ይነግሳሉ።
11.   ማድመጥ፤ ማዬት፤ ማጥናት፤ አዲስ ሃሳብ ዕውቅና ይሰጣቸዋል፤ ይከበራሉ፤ ቀን ይወጣላቸዋል።
12.   ባለቤት አልባ ሁነቶች ከከርሰ ምድር በታች ያሉ የኢትዮጵያ አንቱ ጥሪቶች ሳይቀሩ ለብቃት አቅም የሚሆኑበት ሁኔታ ይመቻቻል። በትጋትና በተከታታይነት ይሰራበታል።
13.   የግል አንባገነንነት ተጥሶ የወል አመራር በግል ሃላፊነት ድርሻ ይሰክናል። እያንዳንዱ በግል ሁሉም በጋራ ይጣመራሉ። ግንኙነቱ መርሃዊ እንጂ ጎናዊ፤ ወይንም ዲያጎናላዊ አይሁንም።
14.   ሃላፊነት በአግባቡ መወጣት የመጀመሪያው ረድፈኛ ሞቶ ይሆናል።
15.   የኢትዮጵያ ሁልአቀፍ ችግር በሰከነ ጥናት፤ በታቀደ ተደሞ አድማጭ ያገኛል። መንገዱም ይጠረጋል። 
16.   „ድሃ፤ ለማኝ፤“ የምንባለበት ዘመን ለመቀየር የመነሻ ነገሮች ይሠራባቸዋል። ለምሳሌ የካቢኒ አባላት ብቃት፤ ጥራት፤ ችሎታ በፓርቲ፤ በዞግ፤ በሌላም ሌላም ሳይሆን በጭንቅላት እና በተጨበጠ የማድረግ ሙሉ አቅም፤ ከሙሉ ጨዋ ስብዕና ጋር ይሆናል።
17.   ለዬዘርፉ ተተኪ ማፍራት ዋናው አናት ጉዳይ ይሆናል። 
18.   በጠ/ሚር በዓለም አቀፍ መድረክ ሳይቀር መሳቂያና መሳለቂያ የሆንበት ዘመን ያከትማል። አንገት አንደፋም። አናፍርም። ወቀሳ አይኖርም ማለት ግን አይደለም። ሁሉን ሰው ማስደሰት ስለማይችል። ኔጌቲብ የሚያስቡ ሰዎችን የመቀነስ ተግባር ተመጣጣኝ ለማድረግ ይሰራበታል። ጥሞና የሚጠይቁ ውስብስብ የተከመሩ የዘመናት ችግሮችም ስላሉብን ግን ሸክሙ ግዙፍ ነው። ተጋድሎውም ግዙፍ ነው። ለዛውም ሀገር ምድሩ ቁጡ በሆነበት ሰዓት። ትእግስት ከእዮብ መሸመት ግን ግድ ይላል። ልቡ ከኖረን። የሚታዬው ግን ዕድሉ የጨበራ ተዝካር ሆኖ ባክኖ እንዲቀር የታደመበት ይመስላል። ሴሪሞኒያዊ ሩጫው ደርቷል። ቀውስ ለመፍጠርም እየተሰራበት ነው። ለኢትዮጵያ እናት ምን ሲቸግር ለኢጎ ብርንዶ ለዛውም የሰው ሳታክት ታቀርባለች። የትውልድ ብክንት ስለመሆኑ ከቁጥር አይገባም። ስከነት ተሰደደ …  
19.   ኢትዮጵያን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚመኟት ሁሉ ልካቸውን ይዘው፤ በመከባባር እና በእኩልነት ላይ ግንኙነቱን እንዲያደርጉ መንገድ ይጀመራል። የውስጥ አርበኛ ሰላዮቹን ጨምሮ ትኩረቱ ከውስጥነት ይሆናል።
210.   ዘመን ጠገቡ የኤርትራውያን ገብተው የማነኮር አዚም ለመጀመሪያ ጊዜ ያከትማል። ኢትዮጵያ በማህጸኗ ፍሬዎች በተቆርቋሪነት ጣዝማ እንደ ተፈጣሯዋ ውሰጧ በፍሬ ዘር ይለመልማል። ወዘተ ወዘተ ወዘተ ገራሚው ነገር አንድ አብይ ብቻ አይደለም ብዙ ናቸው፤ የገድአንባው መንፈስ የተከደነ ሲሳይ ነው። 
·         አንጎል።
ሌላው አቦይ በረከት ስምዖን ደህና መዳራቸውን ባላውቅም ጨርቃቸውን ጥለው የሚያሳብዳችው ነገር ተከስቷል። የኔዎቹ --- ታስታውሳላችሁ አይደል? በባህርዳሩ ኮንፈረስ ላይ ትውር አላሉም የኦሮሞ እና የአማራ የመንፈስ ተደሞ ላይ። ከጎንደሩ ላይ ግን ሙሉ የወያኔ ሃርነት ማንፌሰቶ ባላንባራሶች ተገኝተው ነበር። ግን ለምን? ስለምን? ወፊት ትጠዬቅ … 
  • ·         የጎንደሪት ሙሉቀን።

በዚህ OBN በሠራው የዶር አብይ አህመድ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ቀደም ብዬ እንደ ገለጽኩት ጨርቃቸውን ጥለው አለማበዳቸውም እሳቸው ሆነው ነው - አቦይ በረከት ስምዖን። እንዴት በሉኝ? እንዴት ማለት ጥሩ ነው። የማከብራችሁ „የጎንደር መከራ የጠራው አንድ ታላቅ መንፈስ ደግሞ ተከሰተ“ ተመስገን ትበል ጎንደር። ይህም አቦይ በረከት ብቻ ሳይሆን ባለፈው ዓመት ያን መከረኛ ህዝብ ያደረገውን ተጋድሎ እንደ ጎርፍ፤ የሆያ ሆዬ ነገር፤ እዛውም ሊያልፍ የማይችል የመንደርዮሽ ጉዳይ አድርገው ያጣጠሉት የጸሐፊ አቶ አስራት አብርሃንም መንፈስንም ልክ አስይዞ የሚቀጣ ይመስለኛል። ግን ስለምን ይመስለኛል አልኩኝ። ነው እንጂ። በአማራ ማንነት የህልውና ተጋድሎ ምክንያት ወገኖቻችን የቀራንዮ መከራ ተቀብለውበታል። ይህ ለእነሱ ምንም ነው። የሆነ ሆኖ ያ የ43 ዓመት የዕንባ ዶፍ ይመስለኛል ምክንያት ፈልጎ ፈጣሪ እያናገራ ያለው ቅዱሳኑን። የሞራል አባቱ አቦ በቀለ ገርባ እና የግልጥነት የኔታው አቦ ደረጃ ጣፋ „አማራና ኦሮሞ እስር ቤት ነው ያሉት ከአማራም አብሶ ከጎንደር“ ውጪ ሰው የቀረ አይመስልም ነው። የዛን ህዝብ መከራ - ከውስጣቸው ነው የተጋሩት - ቅዱሳኑ። አሁን ደግሞ ከሰሞኒት አንድ የኢትዮጵያ አዱኛ ድንቅ የሃይማኖት አባት „ለጎንደር ማን አለው?“ አሉ ሊቁ ኡስታዝ አባ ራይ አባመጫ። በቴሌቪዥን እኮ ነው እንዲህ ያሉት። ጉድ በል ጎንደርስ አሁን ነው። ይሄን ያክል ከውስጣቸው ገብቷል የነገረ - ጎንደር አሳር እና ፍዳ። ደም መላሽ! የልቤ መሠረት የሆኑ የሃይማኖት አባት። አደራ ይጠንቀቁ! እነዚህ ሰላቢዎች አይታመኑም። አላህ ጨምሮ ጨምሮ ክብሩን፤ ሞገሱን፤ ግርማውን ይስጥልን። እጅግ የማከብረውት ኡስታዝ አባ ራይ አባመጫ የ43 ዓመቷ ጥቁር ለባሽ፤ የዘመኑ ማገዶ፤ እሰረኛ ጎንደርን በቃሽ እንዲላት፤ ይህ ዘመን የመከራዋ መጨረሻ እንዲሆን እባከዎት የተለዬ ድዋ ያሰደርጉላት? አደራ! ከታችም የለጠፍኩትን ሰቆቃ እባከዎት ያደማጡት። እግዚ አብሄር ይስጥልን። ይኑሩልን። https://www.youtube.com/watch?v=TyzkK6btxRM Ethiopia: OBN Documentary - / አብይ አህመድ ማን ናቸው? : Who is Dr Abiy Ahmed? | February 2018የአማራ ተጋድሎ መከራውን ለማድመጥ ላልፈቀደ ሁሉ ፈጣሪ „በአንድም በሌላም እያናገረ ነው።“ ይሄ ነው አቦይ በረከትን የሸረከታቸው፤ የገረደፋቸው፤ የሾከሸካቸው፤ የሰለቃቸው፤ የወቃቸው፤ የለነቆጣቸው። „ለጎንደር ማን አለው?“ ይገርማል። ተመስገን። እናት ሆዲት ጎንደር ምንም እንኳን መከራሽ ባያልቅም እንደ እናት አንጀቱ የጎጃም ህዝብ ፈጣሪ አምላክ ድንበር፤ ሃይማኖት፤ ብሄረሰብ፤ ጾታ ሳይለይ መከራሽን እዬተጋራ ነው ወገንሽ። አይዞሽ እናትዓለም።
·         አቅመ ልሙጥነት። ጭንቁ በጨርቁ።
የአቦይ በረከት ስምዖን መንፈስ አማራነትን መሸከም አይችልም። በፍጹም! ጭንቅ ነው። ቁመናው ልፍስፍስ ነው። አማራነት ፖሰተር አይደል አይለጠፍ ነገር። ቀለም አይደል አይቀባ ነገር። ወይ ቀዳዳ አይደል ማንነት አይወታተፍ። አማራነት የጥርስ መጥቆሪያ አይደል አይጠቆሩት ነገር። ኤርትራዊ በምን ሂሳብ አማራ፤ የአማራ ወኪል አራጊ ፈጣሪ ሊሆን ይችላል? አይሸመት አይሸቀጥ ነገር ደም። ግን ግን አቦይ በረከት ለመሆኑ ደህና አድረው ይሆን? የቀበር ጉድጓድ!
·         እንጂ ….
እኔ „መባቻን“ „መቋሚያን“ „ጣና ኬኛ የቄሮ ወጣቶችን 2 መቶወቹ የአብቹ አርበኛች“ „ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው“ የጸጋዬ ትንሳኤ መሆኑን ስጽፍ፤ በኋዋላም ጥቃቱ ሲበዛ „አብይ ኬኛ ከክፍል አንድ አስከ ስድስት ስጽፍ“ በመጨረሻም ጉግሱ በፈረቃ ሲጠናከር „ህሊናን“ ስኮልም አቦይ በረከት ስምዖን ነገረ አብይ ከዚህ ይደርሳል ብለው አልገመቱም ነበር። ተስፋቸውን ጥለው የተደላደሉበት ነገር ነበር።

·     የሚገርመኝ፤

እኔ ስለ ዶር. አብይ ፎቶ ስመርጥ ጉግል ላይ 500 አይሞላም ነበር፤ ከዛ ወደ 87 ሺህ ከፍ አለ፤ በሰሞኑ አጀንዳ ደግሞ ወደ 114,000 የሚደርሱ ውጤቶች (0.44 ሴኮንድ) በንግግራቸው ላይም ለማገናዘቢያ ስሰራ በእያንዳንዱ ላይ ከ300 – 1500 ነበር ዛሬ ሳዬው 175,379 views ልብ የሚነካ አስገራሚ ንግግር Dr abiy ahmed # mind set

ይህ ማለት እንግዲህ የተለያዬ ሰው ነው በተለያዩ ዩቱቦች የሚለጥፈው፤ በዚህ ስሌት ቁጥሩ የትዬሌለ ነው። በዬቀኑ ነው የምቆጣጠረው። ዊክሊ በዚህ ሳምንት ብቻ ለሦስት ጊዜ ያህል የህይወት ታሪካቸውን በሚመለከት በማጠናከሪያ አስተካክሎታል። ይህ አቅም ኤርትራን ራድ ያልስያዘ ማንን? ትንቀጥቀጥ። ትንዘፍዘፍ!
·         ከእውነተኛው ዴሞክራሲ ልቆ የሄደ ሰብዕና። 
እዮር ሰማይ ላይ ብቻ ሳይሆን በዚህ ቅዱስ መንፈስ ውስጥ አየሁ። ለዛውም ስለእኔ። ተመስገን።
https://www.youtube.com/watch?v=8Z6HexcMHGU „Ethiopia - Dr Abiy ከላይ ስትሆኑ በዛ መነጽር ብቻ ታች አትመልከቱ“ አጠቃላይ የዕድምታውን ጭብጥ ነው እኔ እማነሳው። ሃዘኑ ከውስጣቸው ሲገባ፤ ተቆርቋሪነታቸው ሲያል፤ እዩት ክብረቶቼ የቻላችሁ አዳምጡት። እስቲ የትኛው አለቃ ነው ሃላፊዎችን ሰብስቦ „ አለቃ ስንሆን ሰርቢስ ማምለጡን ረስተነዋል። አስተውሰነው አናውቅም። ብዙ ጉድ አለ ቤት ውስጥ የልጆች ጉዳይ አለባት፤ ፖርሳዋ ገንዘብ ላይኖረው ይችላል፤ በእግሯ ኳትና ስትመጣ …“ ጨርሱት። „ሌላዋ ደግሞሞ ልጇ ታሞባት ልጄ ታሟል ብላ ፈቃድ ስትጠይቅ የተለያዬ መልስ እንሰጣለን፤ የሃኪም ወረቅት ይዘሽ ነይ ወዘተ … ይሄ ቁስ ነው። ልጅ ታመመብኝ እኮ ነው ያለችው። ሰርግ ልሂድ አይደለም። መደንገጥ አለብን ምን ሆነብሽ? ሰርቢስ አለሽ? ገንዘብ አለሽ? እኔ ላድርስሽ ካልልን ምን አለቃ ሆነው? በዬዕለቱ ሰራተኛ በጉንፋን የሚይዘው መጸዳጃው ቤቱ ንጹህ ባለመሆኑ ነው። ግን አለቆች ሄዳችሁ አይታችሁት ታውቃላችሁን?“ ይሄ ለእኔ ከእውነተኛው ዴሞክራሲ በላይ ነው። እራሱ ዕውነተኛው ዴሞክራሲ ይህን ቅድስና አይችለውም። ምክንያቱም አሸናፊው ድምጽ ትክክልም ትክክልም ላይሆን ስለሚችል፤ ተሸናፊው ትክክል ከነበረ ሊጎዳ ስለሚችል። አሸናፊው ትክክል ቢሆንም ተሸናፊውን ሃሳብ አመጣጥኖ ዕውቅና አይሰጠውም። ስለዚህ ተባደግ ነው ለእኔ በግል። የሰዋዊነት የተፈጥሯዊነት ከሆነ ግን ተሸናፊውም እኩል እንክብካቤ እና ክትትል ይደረግለታል። አቋጣሪው አሸናፊው ሃሳብ እራሱ ይሆናል። ብቻ የዶር. አብይ አህመድ ሰብዕና  ደረጃ እና ጥልቀቱ እንዲህ አይነቱን አንጀት አርስ ርህርና የመሸከም አቅም፤ አቅልም የለውም የአቦይ በረከት ሽሁራር የበላው አይዲወሎጂ ሶሻሊዝም። የወረቀት ነበር ነው። ጭካኔ፤ በቀል፤ ቂም፤ መጠፋፋት፤ ኢጎ፤ ሰላም መንሳት፤ አሉታ፤ ማጥድ፤ ማግለል፤ መቧደን፤ ማህበራዊ ኑሮን ማቃጠል ወዘተ ….።
  • ·         ቅንነት በቅኔነት።

ሌላው ሊቀ ሊቃውነቱ የአቶ ለማ መግርሳ ምጡቅ የግንዛቤ አድማስ ልቅና ብስለት ደግሞ የድርጅቱን ቅኔ እንድናጠናው፤ አንድንማረው ግድ ይላል። አይተነውም፤ ጠብቀነውም የማናውቅ አዲስ ዓለም ነው ትዕግስቱን ከሰጠን። ሥራ አስፈጻሚው ብቻ አይደለም፤ የማዕከላዊ ምክር ቤቱ አባላትም የምርጥ አቅም ወጥ ህሊና ነው እኔ እያዬሁት ያለሁት። ግን „7 ዓመት ታውራ የኖረች ዓይን አንድ ቀን እደሪ ብትባል እንደምን ብዬ አለች“ ይባላል። የአቅል አቅም አነሰን። አዜኔታ አጣን። የታሰረ ለማስፍታት ስንት ጭንቅ እያለ አዲስ ታሳሪ እንማርታለን። አዲስ ለቅሶ እንደራጃለን። አንተላለፋለን። ወጀብ ሲኖር ተግ ብሎ ማሳለፍ ማንን ይገዳል። ጫና አበዛንባቸው። ሁልጊዜ ጥሬ። ግን እኛ ምን ጉዶች ነን?
  • ·         አረስርስ።

ትውልድ የማይተካቸው አርቲሰት ዶር አሊ ቢራ ደግሞ „ለተጨቆነው ህዝባችን መዳሃኒት መሆን አለብን“ ይላሉ። እሰቡት ጥልቀቱን „ለተጨቆነው ህዝባችን“ ነው። ነጻነት አልነበረንም ነው። ጥልቅ ነው ይሄ በጣም። የውሸቱ የሶሻሊዝም ቅርናታዊ ኑሮ አክትሞ እውነተኛ ነፃነት የአብይለማ መንፈስ ያመጣል ነው የሚሉት። መታመን! እና ስለእኛዊነት መልካም ማለም …  እና የኔዎቹ አቦይ በረከትን ቃርሚያ ይሄ ያላሳበደ ማን ይበድ? የደከመች፤ የሰነፈች፤ ኢትዮጵያን ለማዬት ጎንደርን አከርካሪውን መስበር ህልሙ ሆኖ ላደገ የጥላቻ ጥቅርሻ መንፈስ ተዚህ የሚለጥቀው እብደት ወይንም ስደት …. 
  • ·         ጀባ።

በተረፈ ለጥቃችሁ ይህችን ታደምጡ ዘንድ በቅኒት መንፈስ ሰጥቼ ሽው ልብል። ግን ግን ዛሬ ደግሞ አዲስ ሙዚቃም ወጥቶላቸዋል። ግን አስፈራኝ ምን ይሆኑ ብዬ? ምንስ ይነጥቀን ብዬ። በዚህ ነፍስ ውስጥ ቅኖችን ሁሉ አሰብኳቸው። ፈሪ ነኝ እኔ … ኤርትራን ያህል ደመኛ ተሸክመን ፈሪ መሆን ግድ ይላል። ሌላ ሐገር አያሰጋም። ደጋግሜ አንደምጽፈው ኤርትራ እና በረከት ግን አይተኙላቸውም። በፍጹም። መግቢያቸው አይታወቅም። በዬዘመኑ ሚስጢራትን ገብረናል። ሌላ ምን ነበር? አዲስ ነገር ያገኘሁት መረጃ … ትግረኛ ቋንቋ ደግሞ ይችላሉ። ይህም ማለፊያ የምስራች ነው። ቋንቋ ሙያ ነው። ተጨማሪ ዕውቀት። የልብ ለልብ ሃዲድ መዘርጊያ። ቋንቋ ፍቅርና መታመንም!
  • ·         ክወና።

በዝግታ መራመድ ያስፈልጋል። የቅንጅትን የመንፈስ ዲታነትን ቀብረን፤ ኪሳራውን አስከጓዙ መከረኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ተሸከመ። ይሄኛው ከቅንጅትም በላይ የ አቅም ጥሪት ብቻ ሳይሆን የመምራት አቅም በጥበብ የተቀለመ ነው። ድርጁ ነው።  የብልህነት ጥልፍ። አሁን ደግሞ የተደላደለውን ዲታነት አንዳናሾልክ እንጠንቀቅ። ረጋ እንበል። አደብ እንግዛ። ልብ ይስጠን መድሃኒትዓለም አባቴ።
·         የልባዊነት ምርኩዝ።

Ethiopia Dr abiy ahmed በመጀመሪያ ካፖርትህን አዉልቅ

https://www.youtube.com/watch?v=qD9EeCFEraA&t=87s

stic news

Ethiopia Dr abiy ahmed በመጀመሪያ ካፖርትህን አዉልቅ

Ethiopia - New Dr Abiy - አንድ ሰዉ ብቻዉን መለወጥ ይችላል!

https://www.youtube.com/watch?v=0IJZIQdb3Uc

Dr. Abiy Ahmed - አዲሱ ትውልድ ምን አድርጓል?

Abiy Zema - New music Video 2018 - Dedicated to Dr. Abiy Ahmed Ali

·         የእንባ መንኩሲያዋ ጎንደር።

http://www.satenaw.com/amharic/%E1%8C%80%E1%8C%8D%E1%8A%95%E1%8A%90%E1%89%Bጀግንነት አይሰማኝም፤ ጀግና የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፡፡” (ወይዘሮ እማዋይሽ ዓለሙ)

Must Listen Nigist Yerga With Ayalew Menber 2018

VOA Exclusive Interview with Bekele Gerba & Dejene Tafa | Special Report | Ethiopia | Oromo | Amhara




  

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።