"እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች የሚበያረታ"

    

      ነገም ትዘልቂያለሽ።


    „እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች የሚበያረታ በኮረብታዎችም የሚያቆመኝ እግዚአብሄር ነው።“  

                        (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፲፯ ቁጥር ፴፫)  

                  ከሥርጉተ ሥላሴ 07.05.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)







ነገም ትዘልቂያለሽ።
     *****

እኔን ያስደሰተኝ  - ፍጥረተ-ነገርሽ
ጥብቅና መቆምሽ - ለዛች ለእስትንፋስሽ።
ቀጨሬ መጨሬ፤ - ምናምንቴን ትተሽ
አርቲውን ቡርቲውን - ወደ ጎን አድረገሽ፤
ሁለመናሽ  ጠርቶ ጻዳማ ሆነሽ፤
ትናንትም የነበርሽ፤ - ነገም ታብቢያለሽ።
እንዳበራሽ ፀሐይ፤ - ነገም ትዘልቂያለሽ
ዕውነት ለዝንታዓለም ፀድቀሽ ትኖሪያለሽ።


·       ተጣፈ ---- 1985 ዓ.ም ድል ገብያ ገብርኤል አዲስ አበባ።
·       ከመክሊት የግጥም መድብል መጸሐፌ የተወሰደ።






አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።