ልጥፎች

ከማርች 24, 2021 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የወሌሌ ገበታ እና ጠቅላይ ሚኒስትርነት።

ምስል
  እንኳን ወደ ከበቡሽ ብሎግ መሰላም መጡ። ዕለተ ሮብ ማዕዶተ ተናኜ በከበቡሽ የቁራሽ አንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝማራ ለራህብ የሚራራ „ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁኝ“ (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ 3 ቁጥር 17) ·         የወሌሌ ገበታ እና ጠቅላይ ሚኒስትርነት። የእኔ ሃሳብ ከሌላው የተለዬ ነው። በጦርነቱም፤ ጦርነቱን ለማስነሳት የነበሩ ቅድመ ጉዝጓዝ ሁኔታዎችን አስመልክቶም ለዬት ያሉ ሃሳብ ነው የነበረኝ። እራሱ አቶ ሴኩትሬ የማን ነበሩ የሚለው መልስ የሚሻ ጥያቄ ነው። በ ኦነጋዊው ኦህዴድ ሰበር ሳይዋጡ እርጋታን ይጠይቅ ነበር ሁሉም ነገር። ከመቀደም ለመቅደም። ጦርነቱን አስመልክቶ ከብዙ ወዳጆቼ ጋር ተለያይተናል። አንዳንዶቹ የኦህዴድ ጥጋብ ፕሮፓጋንዲስት እንድሆንም ጠይቀውኝ ነበር። ድፍረቱ ቢገርመኝም። በምን ታምር? በምን ቀመር ሥርጉተ ሥላሴ የሄሮድስ መለስ ዜናዊ ቅራሪ ልቅላቂ ፕሮፖጋንዲስት እንድትሆን እንደታሰበ አሁንም ይገርመኛል። ወይ ልክን አለማወቅ። ይህም ሆኖ መዳን አለ ብለን „ኢትዮጵያዊነት ሱሴ“ ሲባል እኮ ዕድሉን ሰጥተን አይተነዋል። የሆነ ሆኖ ከጦርነቱ ዋዜማ ጀምሮ ዞር ብላችሁ ፕሮፋዬሌ ላይ ብትበረብሩ ታገኙታላችሁ። ከጦርነት አመድ እና በቀል ብቻ ነው የሚተርፈው። በጦርነት አሸናፊም ተሸናፊም የለም። የሰሜን ፖለቲካ ድቅትም ነው። በጦርነት በዓይኔ ያዬሁትን ሁሉ በዝርዝር ጽፌያለሁኝ። ከሁሉ በላይ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይን ያመነ ጉም የዘገና ብዬ ሁሉ ጽፌያለሁኝ። ለውጩ ዓለም እኮ የአማራን ሊቃናት ፈጅተው አማራ ሥልጣን ሊገለብጥ ነበር ብለው ሪፖርት አድርገዋል። ለጎረቤት አገሮችም እንርዳችሁ ተብለን ተጠይቀን በቁጥጥር ሥር አውለናዋል አልናቸው ብለው ነግረውናል። ያን ጊዜ

ሕይወት የጥያቄ እና የመልስ ጭማቂ ናት። (24.03.2021)

ምስል