ልጥፎች

ከጁላይ 13, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ

በጎንደር ከተማ የመስቀል በዓል ዕለት “የፈራ ይመለስ”የሚል ቀይ ጽሁፍ የታተመባቸው ቀያይ ቲሸርቶች የለበሱ ወጣቶች ተቃውሞ ሲያሰሙ ዋሉ October 1, 2015, 8:42 am

  በጎንደር ከተማ የመስቀል በዓል ዕለት “ የፈራ ይመለስ ” የሚል ቀይ ጽሁፍ የታተመባቸው ቀያይ ቲሸርቶች የለበሱ ወጣቶች ተቃውሞ ሲያሰሙ ዋሉ October 1, 2015, 8:42 am የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ )  በክርስትና እምነት ተከታዮች የመስቀል በዓል ዕለት የጎንደር ከተማ “ የፈራ ይመለስ ” የሚል ፅሁፍ የታተመባቸው ቀያይ ቲሸርቶች በለበሱ ወጣቶች ተጥለቅልቃ ከፍተኛ የሆነ አመፅን አስተናገደች   ጎንደር ከተማ ( ፎቶ ፋይል ) 2015 የጎንደር ከተማ ለውጥ የሻቱ ወጣቶች ከ 500 በላይ የፈራ ይመለስ የሚል ፅሁፍ የታተመባቸው ቀያይ ቲሸርቶች አሳትመው በማሰራጨት በጎንደር በከፍተኛ ድምቀት በየአመቱ መስከረም 17 ቀን የሚከበረውን የመስቀል በዓል ለመታደም ደመራው ወደ ሚለኮስበት መስቀል አደባባይ ይተማሉ፡፡ ቀጥሎም ደመራው የሚለኮስበት መስቀል አደባባይ ከምዕመኑ ቁጥር ባልተናነሰ ሁኔታ በፌደራልና በልዩ ኃይል የህወሓት ፖሊሶች ተወሮ በማግኘታቸው የደመራውን በተለመደው ሰዓት አለመለኮስ በምክንያትነት በመጠቀም በአምባገነኑ የህወሓት ዘረኛ አገዛዝ ላይ ተቃውሟቸውንና በጉልበት አንገዛም ባይነታቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልፀዋል፡፡ የህወሓት ፌደራልና ልዩ ኃይል ፖሊሶች ለአገዛዙ ያላቸውን ጥላቻና ተቃውሞ የገለፁትን “ የፈራ ይመለስ ” ያሉ ባለቀያይ ቲሸርት የጎንደር ወጣቶችን በቆመጥና በአፈሙዝ በብርቱ በመደብደብ ተቃውሞውን ለማርገብ ሞክረዋል፡፡ በመሆኑም በወጣቶቹ ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች በርካታ ምዕመናን ላይም ጉዳት ደርሷል፡፡