ልጥፎች

ከዲሴምበር 4, 2020 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የፓርላማ የጠቅላዩ ውል ውይቡ የኢትዮጵያ እናቶች ፍቅረኛነት። መደምደሚያ።

ምስል
  እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ። „የሰው ልብ መንገድን ያጋጃል፤   እግዚእብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ምሳሌ 16 ቁጥር 9 የ ፓርላማ የጠቅላዩ ውል ውይቡ የኢትዮጵያ እ ናቶች ፍ ቅረኛነት። መ ደምደሚያ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie   ምንጭ። https://www.youtube.com/watch?v=I-43KpkmB24  መግቢያ። በቅድሚያ እንዴት ከረማችሁ የቀንበጥ ብሎግ ታዳሚዎች። ባለመቻል ከ ዓመት በላይ አልተገናኜነም ነበር። ፌስቡክም አስነፈኝ። ባለፈው ዓመት ጥቂት ሞክሬ ግን ፍጥነቱ የፌስቡክ ገዛኝ እና በዛ አነበልኩኝ። እናት ወሮ ቀለብ ስዩም።                           ወታደር ፋሲል ጌትነት። አሁን ወደ ሙግቱም ተመልሻለሁኝ። ይልመድብሽ ሥርጉትሻ ብያለሁኝ። በህይወት ኑሬ በድጋሜ በመገናኜታችን ደስ ብሎኛል። ምንም እንኳን የ አገራችን ሁኔታ ብዙም የሚያስደስት ነገር ባይኖረውም። ዳንኤሏ ኢትዮጵያ በውነቱ ጸሎት በእጅጉ ያስፈልጋታል። ኢትዮጵያ አሳቻ መንገድ ላይ ናት ያለችው። እሱ አንድዬ ይሁናት እንጂ። አሜን።፡ ·          እ ምምም።   አያፍሬው ጠቅላይ ሚኒሰተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ እናቶችን ልጆች አልባ ሲያደርጉ የባጁበትን ትርክት ሃራም ብለው ተቆርቋሪ ሆነው መጥተዋል። ይህንማ ቀደም ባለው ጊዜ አብይ የኢትዮጵያ ሴቶች ዋቢ የተባሉበትን ማገዶ አድርገውታል ለዞግ በቀል። ተስፋዬም እንዲሁ።     የጋንቤላዋ እናት ላቀረበቸው ጥያቄ እኔ „ሥልጣን ስይዝ ችግር ከመጣ ስወርድ ይቀላል“ ብለው የተሳለቁት ጠቅላይ ሚኒሰተር አብይ አህመድ፤ በቡራዩ፤ በአዲስ አበባ፤ …   በለገጣፎ ለገዳዲ፤ በሰበታ፤ በአርሲ ነገሌ፤ በአሰብ ተፈሪ፤ በሐረር፤ በቴፒ፤ በጉራ ፈርዳ፤ በደንቢ ደሎ