የፓርላማ የጠቅላዩ ውል ውይቡ የኢትዮጵያ እናቶች ፍቅረኛነት። መደምደሚያ።

 

እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ።

„የሰው ልብ መንገድን ያጋጃል፤

 እግዚእብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“

ምሳሌ 16 ቁጥር 9

ፓርላማ የጠቅላዩ ውል ውይቡ የኢትዮጵያ ናቶች ቅረኛነት። ደምደሚያ።

ሥርጉተ©ሥላሴ

Sergute©Selassie

 

ምንጭ።

https://www.youtube.com/watch?v=I-43KpkmB24

 መግቢያ።

በቅድሚያ እንዴት ከረማችሁ የቀንበጥ ብሎግ ታዳሚዎች። ባለመቻል ከ ዓመት በላይ አልተገናኜነም ነበር። ፌስቡክም አስነፈኝ። ባለፈው ዓመት ጥቂት ሞክሬ ግን ፍጥነቱ የፌስቡክ ገዛኝ እና በዛ አነበልኩኝ።



እናት ወሮ ቀለብ ስዩም። 
                         ወታደር ፋሲል ጌትነት።


አሁን ወደ ሙግቱም ተመልሻለሁኝ። ይልመድብሽ ሥርጉትሻ ብያለሁኝ። በህይወት ኑሬ በድጋሜ በመገናኜታችን ደስ ብሎኛል። ምንም እንኳን የ አገራችን ሁኔታ ብዙም የሚያስደስት ነገር ባይኖረውም። ዳንኤሏ ኢትዮጵያ በውነቱ ጸሎት በእጅጉ ያስፈልጋታል። ኢትዮጵያ አሳቻ መንገድ ላይ ናት ያለችው። እሱ አንድዬ ይሁናት እንጂ። አሜን።፡

·         ምምም።

 አያፍሬው ጠቅላይ ሚኒሰተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ እናቶችን ልጆች አልባ ሲያደርጉ የባጁበትን ትርክት ሃራም ብለው ተቆርቋሪ ሆነው መጥተዋል። ይህንማ ቀደም ባለው ጊዜ አብይ የኢትዮጵያ ሴቶች ዋቢ የተባሉበትን ማገዶ አድርገውታል ለዞግ በቀል። ተስፋዬም እንዲሁ። 

 የጋንቤላዋ እናት ላቀረበቸው ጥያቄ እኔ „ሥልጣን ስይዝ ችግር ከመጣ ስወርድ ይቀላል“ ብለው የተሳለቁት ጠቅላይ ሚኒሰተር አብይ አህመድ፤ በቡራዩ፤ በአዲስ አበባ፤ …

 በለገጣፎ ለገዳዲ፤ በሰበታ፤ በአርሲ ነገሌ፤ በአሰብ ተፈሪ፤ በሐረር፤ በቴፒ፤ በጉራ ፈርዳ፤ በደንቢ ደሎ፤ በነቀመት፤  በአጣዬ፤ በማጀቴ፤ በከሚሴ፤ በቤንሸናጉል ጉምዝ፤ በባሌ ሮቤ፤ በአርሲ ዶዶላ፤ በደበረዘይት፤ በናዝሬት፤ በአዋሳ፤ …

በአማሮ፤ በደቡብ ባሉ ከተሞች፤ በጉርጂ፤ በወለጋ፤ የእናቶች ዕንባ የልጆቻቸው ደም ጎርፍ የሆነበትን ዘመን ጠቅጥቀው ያን ስላቃዊ ንግግር ለሚያዳምጥ ከጁቢተር ወይንም  ከኡራኖስ መጡ ያሰኛል።

ኢትዮጵያ ከዓለም በአገር ውስጥ መፈናቀል አንደኛ የወጣችበት አመክንዮው ምን ይባል? ሲፈናቀሉም፤ ሲገደሉም፤ ሲታረዱም፤ ጽንሳቸው ሲወርድም፤ ተገድለው ኩላሊታቸው ሲባልም እያንዳንዱ ልጅ እናት አለው።

ባከዎት ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ሰው ይሁኑልን ብዬ ልለምነወት?

አንዲት ነጥብ ዕንባ እኮ አላፈሰሱም። አላዬሁም፤ አልሰማሁም ብለው ቆስቁሰው ውጭ አገር ሽርሽር ይሄዳሉ። ለሱዳን፤ ለቤይሩት፤ ለጃፓን፤ ለዬመን የሚያዝነው አንጀተወ ለኢትዮጵውያውን ግን ዳሽ ነው።

አንድ ቀን ጥቁር ለብሰው አልታዩም። እራሱ የፓርላማ ውሎ ቀይ ከረባት የሚያስስር አይደለም። ይህ ግፍ የት እንደሚያደርሰዎት እንጃ? ልጅ አለኝ፤ ሚስት አለኝ አባት ነኝ ይሉናል በእርስዎ ዘመን ትውልዱ የከፈለው ሰቆቃ አባትነተዎትን ይሰርዝዋል። ያዬሁት ጭካኔ ነው።

የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስተር ሳሉ አንዲት ሰራተኛ ልጇ ታሞ፤ ትራንስፖርት አጥታ ብትዘገይ ሊከውን ስለሚገባው ሰባዕዊነት የነገሩን፤ ያስተማሩን የት ወሰዱት?

 ሌላ አብይ ነበሩ ይሆን? በሙሉ ሊንኩ አለኝ። ተቀናቃኝወትን  በአምክንዮ ያራገፍኩበት ስለነበር። ዛሬ ደግሞ አውሬ መንፈስ አያለሁኝ። ግን ስንት ሰው ነወት?

ይህ ሁለት ዓመት ተኩል ያዬነው ሰቀቀን፤ አሁንም የቀጠለው ሰቆቃ ለእርስዎ ለምለም መንገድ ነው። ሌላው ቀርቶ አሁን ባለው ጦርነት የስንት ሰው ደጅ ተዘግቷል። አሁን በኢትዮጵያ እኮ ሰው ሙቶ እሬሳ ማንሳት የማይቻልበት ጊዜ ነው ያለነው። ሁላችንም ሱባኤ ልንገባ የሚገባበት ጊዜ።

የሆነ ሆኖ እርስዎ እና የኢትዮጵያ እናቶች ምንም መሰመር ሊያገናኛቸሁ የሚችል የለም።

 የወላይታዋ፤ የጋሞዋ፤ የጉራጌዋ፤ የአገዋ፤ የዶርዜዋ፤ የአዲስ አበባዋ፤ የአማራዋ እናት እሳቸውን መሪዬ ልትል? አላበደችም በአራስ ቤቷ። ሄሮድስ፤ ፈርኦን መሪዬ ተብለው ነበር ይሆን በዘመናቸው?

ለናሙና አንዲት ለኮሮና የተሰጠች፤ ህክምና የተነፈገች እህት ላንሳ። ለምስክርነት። የሳቸው ሸረኛ እና ዘውገኛ ዘመናይ በዬወሩ ሹመት ላይ ናቸው ወሮ አዳነች አበቤ።

አሳርኛዋ የኢትዮጵያ አምሳያ ወ/ሮ ቀለብ ስዩም።

በዘመነ ህዋህት ታሰረች። በረዶ ውስጥ ተዘቅዝቃ ተሰቀለች። አንድ ቀን ብቻዋን ከተወረረወረችብት በጎርፍ ተዋጠች። ብቻዋን ጨለማ ውስጥ የተቆለፈባት ምስኪን ናት እና። 

በጥይት ተኩስ ተከፍቶ በሩ ለ አንድ ቀን አዳር ወደማታውቀው ቦታ ተወስዳ አደረች። ቤቱ ምንም መሰናዶ አልነበረውም ያችን አሳዛኝ ቦታ አይዞሽ የሚልበት። ከቅጣት ወደ ቅጣት።

ህወሃት ክፉ አውሬ ነው። ሞት አይደለም ከዛ በላይም ቢፈረድበት ይገባል።

 የገጠር እናቷ በማያውቁት ዲል ባለው ከተማ አዲስ አበባ የበኽር ልጇን ይዘው 1200 ኪሎሜትር ተጉዘው 6 ጊዜ ተመላልሰው አንድ ጊዜ ብቻ ተፈቀደላቸው። 5ኛው ላይ። ዓይን ለዓይን ስለተገናኙ ጓጉተው ለ6 ጊዜ ሲሄዱ ከለከላቸው ጭራቁ ህወሃት። እስኪበቃው ስለታገልኩት ብቻ ሳይሆን ስልጣኑንም ንጨዋለሁኝ።

አሁን ዝም እምለውም ዝርክርኩ እና ዝልግልጉ የ አብይ አገዛዝ የ አቅም እጦት ነው ብዬ ነው እኔ እማምነው። በጊዜ መከወን ይቻል ነበር።

በሌላ በኩል እነሱም አገር ምሰረታ ላይ መሆናቸውን አሳምሬ አውቃለሁኝ። እነሱም መስፋፋት እና ወረራ ላይ መሆናቸውን በስፋት ጽፌያለሁን። የጨለመበት ባርነት ኢትዮጵያውያንን ይጠብቃል።

 ምልስት ላድርግ ወደ ወ/ሮ ቀለቤ ከዛም በእሷ ምክንያት እኒያ የጅግና ባተሌ እናት አለፉ።

የሚገርመው የቀዳማዊ እመቤት ወሮ ዝናሽ ታያቸው እና የ እሷ ቤተሰቦች አንድ ወንዝ የፈለቁ ናቸው። አንዷ ለዙፋን ሌላዋ ለካቴና።

ወደ ቀደመው ምልሰት ሳደርግ ይህም ብቻ አይደለም የባለቤቷ ወንድም ወታደር ፋሲል ጌትነት ፎቶውን እለጥፋለሁኝ እሷ እንደ ታሰረች የደረሰበት ለ7 ዓት አይታውቅም።

 ይህ በጋብቻ ዝምድና ላይ የሚያስከትለው ቀውስ ከልብ ሆኖ ለመረረመረው ሌላ የተጋድሎ ምዕራፍ ነው ይህ ቤተሰብ የገጠመው። ይህን መሰል ግፍ በስሜን ጎንደር በስፋት በዬቤቱ ተፈጽሟል። ለዚህ ነው የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ ሥር ነቀል ለውጥ የሚያስፈልገው።

ይህን ሁሉ መከራ ያሳለፈች አንዲት በጣም ወጣት ሊቅ ስትፈታ የኢትዮጵያ የሰላም አንባሳደር ሆነች። „እናት ኢትዮጵያ“ የሚል በጎ አድራጎት ድርጅት ፈጠረች፤ አደራጀች። መራች።

አሁን ለድጋሚ ጊዜ እስረኛ ናት። የሚገርመው ጠቅላይ ሚኒሰተር አብይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስተር ከሆኑ የ የኢትዮጵያ ሴቶች ዕንባ ይደርቃል ብዬ የመሰከርኩትም ደርቆ ክው ብሎ ቀረ። አዋረዱኝ።

በዚህ ነው መንፈሳቸውን ለማስጠጋት የሚቀፈኝ። ሰርክ ክህደት። ክህደት ከቁንጮ ሲሆን ትውልዱ ያሳዝነኛል።

ወሮ ቀለብ ስዩም አሁንም እስረኛ ሁና ሳያት ኢትዮጵያን  በእሷ ውስጥ አያታለሁኝ። እንደ ትናንቱ ሁሉ አሁንም ኢትዮጵያ እስረኛ ናትና። አሁን ወሮ ቀለቤን ያሰረ መሪ ስለ ኢትዮጵያ እናቶች ሲያወራ ያስታውካል። ያሳፍራልም።

·         ሆነ ሆኖ … 

ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድን አብዝቼ ስለተከፋሁባቸው ጭካኔ ከጀመሩበት ከ ኢንጂነር ስመኜው ህልፈት በኋላ እንዲህ በተምስጦ አዳምጫቸው አላውቅም። ለዚህም ነው ሙግቱ ተግ ብሎ የባጀው።

በትናንት የፓርላማ ውሎ ግን በቀደመው አቅሜ ልክም ባይሆንም ጦርነት እና ኢትዮጵያ ስለሆነ አዳመጥኩት። ለዛውም ደግሜ። እናም ሞገትኩት።

እርገት ይሁን።

ሰሞኑን የትኛውም ሚዲያ ያለውን አቋም ሆነ ዕይታ አላደመጥኩትም ነበር። ተጽዕኖ እንዳይፈጥርብኝ። ዛሬ ካቻልኩኝ አዳምጠዋለሁኝ። ምን እንደ ተሰማቸው።

በተለይ በአማራ ፋኖ፤ በአማራ ሚሊሻ፤ በአማራ ልዩ ኃይል፤ በአማራ ህዝብ ሙሉ ብቁ የተሳትፎ ልቅና፤ በአማራ እናቶች ክህደት ላይ የሚዲያውንም ሁሉ ስሜት ማወቅ እሻለሁኝ። ሁሉም መሰረቱ፤ ጉዝጓዙ ቅኑ አማራ ነውና።

የእኔ ቅኖች።

 

ከክፍል አንድ እስከ ክፍል 8 ድረስ ፌስ ቡኬ ላይ አለ ሙግቱ። እንደ ጤፍ እንጀራ ዝንጥፍጥፍ ያለ ምስጋናዬም፤ ክብሬንም በሞገስ ይድረስልኝ ለቅኖቹ ለአገሬ ልጆች። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ኑሩልኝ። ቸር ወሬ ያሰማን። አሜን። መሸቢያ ጊዜ።

 እናቶችን በበዛ ሁኔታ የበደለ ሄሮድስ በምን ሞራል ይክስ ይሆን?

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።