ለእስር ጊዜ ሦስት ዕጥፍ ቀረጥ መክፈል።
ሌላ ግፍ ለእስር ጊዜ ሦስት ዕጥፍ ቀረጥ መክፈል ግድ ነው። ከሥርጉተ ሥላሴ 17.08.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) „ህልም ከመሆን ወዳለመሆን ይሄዳል በዬምሳሌውም እዬራሱ ያሳያህል።“ (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፩ ቁጥር ፫) መቼም ተችሎ የተኖረው ጉድ ምን ይባል? ማን ይባል? አይታወቅም? ያው የደብረታቦር እና የባህርዳር ጉባኤ እጅግ የተመሰጥኩበት ስለሆነ ዛሬ ደግሜ ማድመጥ ፈልጌ አማራ ቴሌቪዥን ላይ አገኘሁት። ለካንስ ትናንት ከተለጠፈው የተቆራረጠ ስለነበር ነው መሰል ዛሬ ደግሞ ሙሉውን አገኘሁት። ግርም ብሎኛል። ለካንስ የእስር ጊዜም ቀረጥ በሦስት እጥፍ መክፈል አለበት አንድ እስረኛ። ያ ቀረጥ እዚህ እስር ቤት አልነበርኩም። እንግልትም አልደረሰብኝ ብሎ ነው። ወዲህ ነው ነገሩ አንድ እስረኛ አንድ ዓምት ከስድስት ወር ከታሰረ ሲፈታ ታስሮ ነበር ተብሎ የሚሰጠው የእስረኝነት ማረጋገጫ የፍዳ ዲግሪው የሦስት ወር ብቻ ነው። ሦስት ወር ታስሮ ነበር የሚል ምስክር ወረቀት ብቻ ነው የሚሰጠው። የደገምኩት እንድታምኑት ነው። የአንድ ዓመት ከሦስት ወሩ የቆጥ የበረከቱ ለወያኔ ሃርነት ትግራይ መሳፍንታት ቆሌ መቋደሻ ነው። እዚህ እስር