ልጥፎች

ከኤፕሪል 9, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አሸባሪው ማን ነው? አቶ አባይ ወልዱ ወይንስ ዬአማራ ተጋድሎ አክቲቢስት ወጣት ንግስት ይርጋ? ከሥርጉተ ሥላሴ 21.01.2017 (ዙሪክ - ሲዊዘርላንድ)

ምስል
  • ዬአማራ ተጋድሎ ሲነሳ ዬፃፍኩት ነው። ዛሬ 09.04.2023 አመት ድገም እያለን ነው። • አሸባሪው ማን ነው? አቶ አባይ ወልዱ ወይንስ ዬአማራ ተጋድሎ አክቲቢስት ወጣት ንግስት ይርጋ? ከሥርጉተ ሥላሴ 21.01.2017 (ዙሪክ - ሲዊዘርላንድ)     „እንደ ጠቢብ ዬሆነ ሰው ማነው? ነገርንስ ዬሚያውቀው ማነው?" (መጸሐፈ መክብብ ምዕራፍ ፰ ቁጥር ፩) ይድረስ ለወያኔ ሃርነት ትግራይ መሪዎች። ትግራይና አዲስ አበባ። • እፍታ። ያለለት ሃቅ - ትነጥራለች። ያለለትም ውንብድና - ይቆማል። ያለለት ዬምድር ዕንባ ለፍሬ - ይበቃል። ያለለት ዬአፓርታይድ ግዛት መቃብር - ይበላዋል። ያለለት ጥጋበኞች ዬማዕት አውሎ - ይውጣቸዋል። ያለለት ዬዕንባ ቤተኞች መከራቸው መከውኑን ምክንያት አድርገው አምላካቸው ስላደረገላቸው መልካም ነገር ሁሉ በተመስጦና በቀስታ ያመሰግናሉ። ይህ ከምድራውያን ዬሚጠበቅ ዬራፊ ጸጋ ሳይሆን ዬዕንባ አድማጭ ከሆነው ከፈጣሪ ደጅ ብቻ ዬሚታፈስ፤ በውለታና በጉቦ ዬማይደፈር ሰማያዊ በረከት ነው። በሰው እጅ በመቁንን ተለክቶ በአድሎ - ዬማይደለደል። መክሊት። እራሷን ለበላህሰቦች ዬማገደች ወጣት ናት። አዎን በአማረነቷ ዬሚደርሰው በደል ልኩን ስላለፈ - ፊት - ለፊት ወጥታ ዬወያኔ ሃርነት ትግራይን ማንፌስቶ አንጎል ዬሞገተች ድንቅ ፍሬ ናት። ዬአማራ ጉዳት ዬማይሰማው አካል በግማሽ ግድግዳ ቤትን እንደ መገንባት ስለማሰብ በመሆኑ፤ ሙሉ አቋም ላይ ዬሚገኝ ዬጋራ ቤት እንዲኖረን ዬራሷን ዬቤትሥራ ዬተገበረች ዕንቁ ናት። ዬአማራ መከራ እንደ አልባሌ ማበሻ ጨርቅ ካልተወረወረ … ብሄራዊ ጀግናችን ናት። እንደ ህዝባዊና ሙያ ማህበራት አደራጅነቴ ደግሞ ዓይኔ ናት! ብርቄ ናት! ናፍቆቴ ናት! መሪዬ ናት! • ምልክት። ለወያኔ ሃርነት መሳፍንት ሦስት ምልክቶ

Thank you for your letter dated 30 March 2015 suggesting that love should be an integral part of society in order to contribute to meeting the challenges that are world

ምስል
  EUROPEAN COMMISSION DIRECTORATE-GENERAL FOR EDUCATION AND CULTURE Modernisation of Education If: Education policy and programme, Innovation, EIT and MSCA International cooperation in education and youth; Jean Monnet actions Brussels, Seble Weldetencay Winterthur, Switzerland Email: smeklete@yahoo.com Re: Your letter to President Juncker Dear Mr Weldetencay,   Thank you for your letter dated 30 March 2015 suggesting that love should be an integral part of society in order to contribute to meeting the challenges that are world is facing, in particular in families, culture and education. We of course can only support this notion and do believe that taking care of others can be translated into a number of initiatives. Youth Volonteering for instance is one, important, form of showing care for others and competence-based programmes in schools and universities also help by giving students new skills, ethical skills, working as a group, the respect of socio-cultural diversities and generall

Feedback Sendung und Website „Tsegaye" Von Solomon A. Getahun, PhD Central Michigan University Dear Radio LoRa Team

ምስል
  Feedback Sendung und Website „Tsegaye" Von Solomon A. Getahun, PhD Central Michigan University Dear Radio LoRa Team From what I read and listened on the website; it is not religious. However, the web designer and host are apparently masters of the Amharic language. They are also very well versed in Geez, the ancient language of Ethiopia, which the Ethiopian Orthodox clergy solely uses as liturgical language.    Therefore, the webhost uses of archaic Amharic interlaced with Geez seem to give the website a religious appearance (no one uses old Amharic and Geez words in day-to-day communication) but not in reality— as one can see from the content of its program and context of its presentation. There is nothing sexist about the site. Nor does it represent a certain ethno-linguistic group. Yet, the webpage is designed with green, blue and red colors, the try-colors of Ethiopia, which, once again, seems to give the impression of nationalistic and for some, ultra-nationalistic appearan

#አንሰበርም! ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 06/04/2023 #ቫወል አንሰበርም!

  #አንሰበርም ! ለሰማእታቱ የአማራ ልዩ ኃይል አባላት እና ቤተሰቦች ከልብ ዬተሰማኝን ሃዘን እገውፃለሁኝ። ከፋሽስታዊው ሥርአት የሚጠበቅ ነው። በህግ እና በሥርዓት ተፋልመን ደረጃውን ልኩን አውቆ እንዲራመድ ለማድረግ የሚገባነን እንሠራለን። እናደርጋለንም። ኢትዮጵያ ያላችሁ ወገኖቻችን ዞር ማለትን ልመዱ። በርደኑን እኛ እንሸከማለን። ሚዲያ ላይ ያላችሁ ደግሞ እርእሱን ተራጋጭ አታድርጉት፤ መፃፊያ ቀለሙን አታንቀልቅሉት። ዬአማራ ልዩ ኃይል ከመንግሥት አፈነገጠ ይላል የኢትዮ 251 ሚዲያ። ማንን ይጠቅማል ምንስ ያተርፋል? ቀለሙ ቢጫ ነው ጥሩ ነው። በምንም ሁኔታ ቀይ ቀለም አያተርፍም። ሰማያዊ ቢጫ መጠቀም ይበጃል። አረንጓዴም ሸጋ ነው። ወጣትነት ከጨካ ሥርዓትን እፋለማለሁ ሲሆን ከባድ ነው። ወጣቶች ወንጀል ቢሆንብኝም ወጣትነታችሁን ተላለፋት። እንደ ዕድሜ ሙሉ ሰው ሁኑ። ሁላችንም ጠብ ለማይል ትግል ወጣትነታችን ተላልፈን ከዚህ ተደርሷል። ቀን አያልቅም። እና ነገን ታዩ ዘንድ በእርጋታ እና በስክነን ታገሉ፤ አታግሉ። መኖር ሁሉን ይሰጣል። ማለፍ ደግሞ መፈጠርን ያጠናቅቃል። ከጎናችሁ ነኝ። አይዟችሁ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 06/04/2023 #ቫወል አንሰበርም!

ኢትዮጵያ በኢመርጀንሲ ሩም። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 06/04/2023 #አንሰበርም።

  ኢትዮጵያ በኢመርጀንሲ ሩም።   😢   መለጠጡን በልክ። እንኩቶ ነኩቶ የትውልድ እንዳማይሆን አውቆ ቢታሰብበን። ጡንቻ ሆነ ጠበንጃ ማሸነፍ አይደለም። ፈጣሪ የእስልምና ሮመዳን ዬእኛ ሁዳዴ አዋዶ ያቀረበው ምክንያት አለው። ኢትዮጵያ በኢመርጀንሲ ሩም ውስጥ ናት። ለዘላቂ መፍትሄ እንተጋለን። ፀሎት፤ እርጋታ፤ ስክነት፤ የአበዱ እሳቤወች ግልቢያን መጠዬፍ፦ እያንዳንዱ የግፋዓን ቤተኛ በተሟላ ሥነ - ምግባር አምላኩን እግዚአብሄርን ሳያስከፋ በልኩ እንደ ልኩ ይጓዝ። አቅም አለን። ጨምተን ሳናባክነው አቅማችን መጠቀም ከተቻለ አያቅተንም። ዝርክርኩን ገርተን፤ ወጣገባውን ልገን በልኩ ልኩን እንዲያውቅ ማድረግ ይቻላል። ዬሚፈሩትን አልጀመርነውም። ስንጀምረው ደግሞ ይሆናል። በሩን ቧ አድርጎ ለጥረታችን ስኬት የሚከፍተው አንድዬ ነው። ቅኖች ነን እና። በዚህ ውስጥ ውዶቻችን እንዳናጠ በጥንቃቄ ተራመዱ። በለት ዬሚሆን ነገር ዬለም። የተደራጀ፦ የተቀናጀ ህሊና ይጠይቃል። ፕሮፖጋንዳ ንፋስ ነው። ንፋስ ደግሞ ወጀቡን ፍጥነቱን ቢጨምረው እንጂ አይቀንሰውም። ብስጭትም ገደል ነው። ተፍ ተፋ አውሬው አቅሙን ጨምሮ ዬበለጠ ጥፋት እንዲያደርስ መጋበዝ ይሆናል። ከግልቢያውም፦ ከትርፍ ንግግሩም፦ ተግ ማለት ያስፈልጋል። አዲስ ነገር ዬለውም። የተለመደው ነው ያገረሸው። በሥነ - ልቦና ቀውስ ዬሚታመሰው ኦነጋዊው ፋሺዝም መጣደፋ የሚጠበቅ ነው። ሰክኖ መጓዝን ይጠይቃል። የእሱን ሰበር እዬቀዱ ሰበር ከማለት። ህወሃት ጋር መስማማት ይህን ያህል ካንጠራራ፤ እንዲያው ሌላ ቢገኝ ምን ሊኮን ይሆን ያሰኛል። እኔ እንኳን አይሞቀኝ አይቀዘቅዘኝ። በጥሞና ሁሉንም ነገር ቀድሜ ገልጫለሁኝ። ሰሚ ጠፋ እንጂ። የሆነ ሆኖ የገዳ መሳፍንታት በልክ ብትሆኑ አሁንም እንነግራለን። "ሲከር መበጠሱን ሲሞላ መፍ

አሉታዊ ዴሞግራፊ ፋሺዝም ነው። የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ጥንስሱ ይኽው ነው። ኢትዮጵያ በይፋ ነው አሉታዊ ዴሞግራፊ የተካሄደው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ

ምስል
  ይህችን ሊንክ እለጥፍልህና ታገናዝበዋለህ። ቀድሜ በብዙ ሞግቻለሁኝ። ዴሞግራፊን እኔ አሉታዊ እና አወንታዊ ብዬ እከፍለዋለሁኝ። አሉታዊ ዴሞግራፊ ፋሺዝም ነው። የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ጥንስሱ ይኽው ነው። ኢትዮጵያ በይፋ ነው አሉታዊ ዴሞግራፊ የተካሄደው። ለአፍሪካም ያሰጋል። ለዚህ ነው እኔ ዛሬ ምንም አዲስ የማይሆንብኝ። ግድ ነው። መፈናቀል፤ ሞት እስራት ስደት። ምክንያቱም የፍልስፍናው ውቅር ይህ ስለሆነ። ስለሆነም በትጋት ሠርቸበታለሁኝ። ዛሬ የተመለሱት ፀፀት የለብን ሲሉ አዳምጣለሁኝ። ሊፀፅታቸው ይገባል። ዲሞግራፊ ላይ ሆነው ዲሞክራሲን ሲጠብቁ። የትኛውም የፖለቲካ ዕሳቤ ከዚህ ነው ሊነሳ ዬሚገባው። ተረኛም አትበሉ ሲል ሰምቸዋለሁ ዛሬ አቶ ግዛው። "ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ" ተረኛ በሚለው ዕሳቤ ዘመኑን አይመጥንም። ቆባ ነው። ፋሺዝም + የገዳ ወረራ፤ የገዳ መስፋፋት፤ ዬገዳ አስምሌሽን እና ዲስክርምኔሽን ነው። ይህ ከውጥኑ ጀምሮ እንዴት እንደሞገትኩት ልብ እና ህሊና ያላችሁ ወገኖቼ አንብቡት። አዳምጡት። #ሊንኮች ። • ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም። - ዲሴምበር 16, 2019 ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም። ከዚያ የከበደ መከራ ላይ ናቸው አላዛሯ ኢትዮጵያም ሆነ እማማ አፍሪካም። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱) ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።   • https://sergute.blogspot.com/search... ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም። • https://www.youtube.com/watch?v=myaY01aP4pg&t=286s የኦሮሙማ ጠቀራዊ የዲሞግራፊ ፋሽስ

#ብስጭትን + ቁጣን ሰክኖ ስለማስተዳደር። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08/04/2023 #አንሰበርም!

ምስል
  #ብስጭትን + ቁጣን ሰክኖ ስለማስተዳደር።     ክብሮች እና ክብሬ ጤና ይስጥልን? እጅ ነሳን ከጭምቷ ቅኒት ቅድስቲት ሲዊዘርላንድ። እንዴት ነን። አይዞን! እርእስ አስቀምጬ ጽፌ አላውቅም። ጽሁፍ ከጨረስኩ በኋላ ነው እርእስ እምሰጠው። ዬሆነ ሆኖ ይሞከር። ከብስጭት በላይ ቃል ካለ ብትነግሩኝ። በአማራ ህዝብ የደረሰው ከብስጭትም ከቁጣም በላይ ቢያደርግ አይደንቅም። ልኩን አልፎ አለመሄዱ ለዓለም ሳይቀር የአማራ ህዝብ ዓለምን ያስተማረበት ተቋማቱ ነው። የአማራ ህዝብ እና ተፈሪ መንፈሱ በዬዘማናቱ ተጫኝ፤ አግላይ ሁነቶች በአንድም በሌላም ተከስተውበታል ብዬ አምናለሁኝ። የአማራ ህዝብ በብሄራዊ ብቻ ሳይሆን በዓለምም ደረጃ የታወቀ የታመቀ ሁነት እንዳለበት ይገባኛል። አልተሰራበትም እንጂ ቢሠራበት የአማራን ህዝብ አንድ ቁልፍ ዕድምታ ያስፈልገው ነበር። ከኢንጂነር ታከለ ኡማ ጋር የቃላት ተርቲም ከመግጠም። ልብ እና ህሊና ፍላጎት እና ምኞት ተግብ ጋር ጋራ ለጋራ፤ አፋፍ ለአፋፍ ማስነው አቅሙ ሁሉ ዬትሜን እዬተበተነ ፈሶ እዬተለቀመ፤ ተለቅሞ እዬፈሰሰ ባልተባከነ ነበር። የሆነ ሆኖ ሁሉም አስተዳዳሪ መሪ ይሻል። ሰውም እንሰሳም መሪ ይሻሉ። ቁጣም፤ በቃም፤ አይም፤ አሻም መሪ ይሻሉ። በስተቀር አናርኪዝም ይፈጠራል። በተለይ በዚህ ዓምስት ዓመት የታዘብኩት መሪወችም አናርኪ ሆነው ነው። #ገዢው ብቻ አይደለም። ተዋህጂ፤ ተቀናቃኝ፤ ተቃዋሚ፤ ተፎካካሪወችም። ተቀናቃኝ ከተፎካካሪ፤፦ተዋህጅ ከተተቀናቃኝ የዕድምታ ልዩነት አላቸው። በ2010 እኢአ ሰርቸዋለሁኝ። አሁን ኢዜማ እና አብን መግለጫ አወጡ ተብሎ እንደ አጋር ሲታዩ ይገርመኛል። አሁን ያለውን ሥርዓት ተቀብለው እያገዙ ዬሚያጠነከሩ፤ ጉልበት የሚያመነጩ አጋር ሳይሆኑ የጀርባ አጥንት ፒላሮች ናቸው። ስለዚህ ጥንካሬያቸው ሆነ ድክ

#በዛሬ ውስጥ ነገን አደላድሎ ስለመምራት ይቻል ይሆን። Ja! ይቻላል! ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08/04/2023

ምስል
  #በዛሬ ውስጥ ነገን አደላድሎ ስለመምራት ይቻል ይሆን። Ja! ይቻላል! "አድርገህኛል እና አመሰግንኃለሁ።"     !እንዴት ይቻላል? #መነሻን አክብሮ በመነሳት ይቻላል። #መድረሻን አክብሮ በማቀድም ይቻላል። #አገናኝ ድልድይ ዘመናትን አዋዶ በመነሳትም ይቻላል። #ትናንትን በዛሬ ማድመጥ ነገን ዛሬን አደላድሎ በማበጀትም ይቻላል። ዊዝደሞቻችን ትናንትን ሳይሞት ያቆዩት እንዴት? በምን ስሌት? ትናንትን ሬሳ ክምር ለማድረግ 50 ዓመት ተጉዘን አመድ እና በቀል ተቸረፈሰ። ታስታውሳላችሁ ጦርነቱ ሲወጠን በጦርነት አትራፊነት የለም። አትራፊ አለ ከተባለ #በቀል እና #አመድ ነው ብዬ ሞግቼ ነበር። ዓለምንም በራሽያ እና በዩክሬን ጦርነት ሞግቻለሁኝ። ይህም ብቻ ሳይሆን ጦርነትን የሚፎካከሩ ተቋማት ከመገንባት የፍቅር ተፈጥሯዊ ህግጋት የሚገነቡ #ክፋ ዕሳቤወችን የሚመክቱ ተቋማት እና ፍልስፍናወች ላይ ይተኮር ሌላው በአጽህኖት የፃፍኩት በአማርኛም በጀርመንኛም ነበር። በሌላ በኩልም ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የአገር መሪ አያደርግም፤ ዬአገር መሪ መሆን ግን ተጽዕኖ ፈጣሪ ያደርጋል ብዬም ጽፌያለሁኝ። ግድፈቱ ብሄራዊ ብቻ አይደለም ሉላዊ ነው። ዓለም ከአናሎግ ወደ ዲጅታል ስትሸጋገር ጦርነት እና መንስኤወቹን የሚመክት አቅም ሳታበጅ ነው። መመከቻ የሃሳብ አቅም የላትም። ሥልጣኔን ሥልጣኔ ሲያወድም የራሽያ እና የዩክሬን ጦርነት በቂ ነው። በብድር በትውስት ርዮት የተቀመረው ማህበረ ኦነግ የተደራጀን ተቋም በማፈርሰ ኢትዮጵያ ዬተበደረችውን ሳትመልስ ዕዳውንም አመዱንም በማውረስ ለትውልድ ሥልጣኔውን ለአመድ ሲሸለም በአገራችን በኢትዮጵያ በገሃድ አይተናል። ለምን? እሬሳ፤ በቀል፤ ቂም፤ ቅናት አንዱ ለአንዱ ስጋት የእኔ ብሎ ካለማድመጥ የመጣ ነው። የዩክሬኑ መሪ በአ