ኢትዮጵያ በኢመርጀንሲ ሩም። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 06/04/2023 #አንሰበርም።

 

ኢትዮጵያ በኢመርጀንሲ ሩም።
 
😢
 
መለጠጡን በልክ። እንኩቶ ነኩቶ የትውልድ እንዳማይሆን አውቆ ቢታሰብበን። ጡንቻ ሆነ ጠበንጃ ማሸነፍ አይደለም። ፈጣሪ የእስልምና ሮመዳን ዬእኛ ሁዳዴ አዋዶ ያቀረበው ምክንያት አለው።
ኢትዮጵያ በኢመርጀንሲ ሩም ውስጥ ናት። ለዘላቂ መፍትሄ እንተጋለን። ፀሎት፤ እርጋታ፤ ስክነት፤ የአበዱ እሳቤወች ግልቢያን መጠዬፍ፦ እያንዳንዱ የግፋዓን ቤተኛ በተሟላ ሥነ - ምግባር አምላኩን እግዚአብሄርን ሳያስከፋ በልኩ እንደ ልኩ ይጓዝ። አቅም አለን። ጨምተን ሳናባክነው አቅማችን መጠቀም ከተቻለ አያቅተንም። ዝርክርኩን ገርተን፤ ወጣገባውን ልገን በልኩ ልኩን እንዲያውቅ ማድረግ ይቻላል። ዬሚፈሩትን አልጀመርነውም። ስንጀምረው ደግሞ ይሆናል። በሩን ቧ አድርጎ ለጥረታችን ስኬት የሚከፍተው አንድዬ ነው። ቅኖች ነን እና።
በዚህ ውስጥ ውዶቻችን እንዳናጠ በጥንቃቄ ተራመዱ። በለት ዬሚሆን ነገር ዬለም። የተደራጀ፦ የተቀናጀ ህሊና ይጠይቃል። ፕሮፖጋንዳ ንፋስ ነው። ንፋስ ደግሞ ወጀቡን ፍጥነቱን ቢጨምረው እንጂ አይቀንሰውም። ብስጭትም ገደል ነው። ተፍ ተፋ አውሬው አቅሙን ጨምሮ ዬበለጠ ጥፋት እንዲያደርስ መጋበዝ ይሆናል። ከግልቢያውም፦ ከትርፍ ንግግሩም፦ ተግ ማለት ያስፈልጋል። አዲስ ነገር ዬለውም። የተለመደው ነው ያገረሸው።
በሥነ - ልቦና ቀውስ ዬሚታመሰው ኦነጋዊው ፋሺዝም መጣደፋ የሚጠበቅ ነው። ሰክኖ መጓዝን ይጠይቃል። የእሱን ሰበር እዬቀዱ ሰበር ከማለት። ህወሃት ጋር መስማማት ይህን ያህል ካንጠራራ፤ እንዲያው ሌላ ቢገኝ ምን ሊኮን ይሆን ያሰኛል። እኔ እንኳን አይሞቀኝ አይቀዘቅዘኝ።
በጥሞና ሁሉንም ነገር ቀድሜ ገልጫለሁኝ። ሰሚ ጠፋ እንጂ። የሆነ ሆኖ የገዳ መሳፍንታት በልክ ብትሆኑ አሁንም እንነግራለን። "ሲከር መበጠሱን ሲሞላ መፍሰሱን" ልሸልማችሁ። መጨረሻችሁ ይናፍቀኛል። ጥጋብም፦ ጥድፊያም፥ መወጣጠርም ሁለገቡ ጥቃትም፦ የሚሰክንበት፦ ምድር ቀውጢ የምትሆንበት ቀን ይመጣል። ተስፋችን አምላካችን።
#አብሮ መደርመስ፤
#አብሮ መፍረስ፤
#አብሮ መትነንም እንዳለ ብታስቡ ጥሩ ነው።
#የአማራ ህዝብ ይነሳል።
#ቅንነቱ እና #አምላኩ #ዬሰመሩ ናቸው እና።
"የቤትህ ቅናት በላይ"
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
06/04/2023

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።