ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 16, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

#የጨመተው ደቡብ እና ስኬቱ። • እቴጌ ጎንደር ሆይ! ከዚህ የብልህነት #ልዕልና ምን ተማርሽ?

ምስል
  • #የጨመተው ደቡብ እና ስኬቱ። • እቴጌ ጎንደር ሆይ! ከዚህ የብልህነት #ልዕልና ምን ተማርሽ?   #ምዕራፍ ፲፯   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።        #መቅድም ።   በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ክስተታዊ ውሳኔ የወሰነ የፖለቲካ ኢሊት የሚገኝበት የደቡብ ክልል ነው። የቀድሞው ጠቅላይ ሚር አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ ብዙወቹ ቁምጥ የሚሉለትን የ፬ ኪሎ የክብር፤ የማዕረግ ሥልጣን፤ የጠቅላይ ሚኒስተርነትን ቦታ በፈቃዳቸው የለቀቁ ታላቅ ሰው ናቸው።    የተከበሩ አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ ለትውልዱ የፖለቲካ ሥልጣን ማለት ከህዝብ ፍላጎት በላይ እንዳልሆነ ተቋም፤ ሐዋርያ ሆነው በተግባር አሳይተዋል። አብነትም ናቸው። በዘመናቸው ለአጎደለቱ፤ ለጠቀሙት ጉዳይ ዘመን የሚፈታው አመክንዮ ነው። እኔ እራሴ ብርቱ ሞጋቻቸው ነበርኩኝ። አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን ካለምንም ቅድመ ሁኔታ መልቀቃቸ ግን የሚያሸልም የልዩ የታሪክ ክስተት መሥራች ናቸው።    #የደቡብ ህዝብ።   የደቡብ ህዝብ ለስላሳ ህዝብ ይመስለኛል። የደቡብ ህዝብ የማይቸኩል ዝግ ያለም ይመስለኛል። የደቡብ ህዝብ ያስተዋለም ይመስለኛል። የደቡብ ህዝብ #ዕድሉን #የማያፈስ ይመስለኛል። ይመስለኛል እምለው ኑሬ ስላላየሁት፤ በጥናትም መረጃውን በዳታ ሰለአላቀነባበርኩት ነው። በኮርስ፤ በሥራ ዓለም ግን ደቡቦችን በተወሰነ ደረጃ አውቃቸዋለሁኝ። ለዚህም ነው #የጨመተ የሚለውን ኃይለ ቃል የተጠቀምኩት።   የደቡብ ህዝብ ኢሊቶች ህዝባቸውን #በመገበር አይታወቁም። የደቡብ ህዝብ የፖለቲካ ኢሊቶች የህዝባቸው የውስጥ ሰላም እንዲታወክ አይፈቅዱም። ይልቁንም መሻታቸውን፤ የት...

የኢትዮጵያ #ኦርጋኒክ ተፈጥሮ #ያልከበዳቸው ሊቀ - ሊቃውንት #የኔታ ኢኒጂነር ጌዲዮን አስፋው።

ምስል
  የኢትዮጵያ #ኦርጋኒክ ተፈጥሮ #ያልከበዳቸው ሊቀ - ሊቃውንት #የኔታ ኢኒጂነር ጌዲዮን አስፋው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       https://www.youtube.com/watch?v=2i3_8noLNN0&t=11s የህዳሴ ግድቡን ዶሴ የያዙት ኢንጅነር https://www.youtube.com/watch?v=b8O3hEhsM0k ግብፆች አንድ ሳተላይት መድበው ይከታተላሉ ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው ‪@ethiopian_reporter‬   #ጠብታ ።   • ይህን ደርባባ የትውልድ የሆነ ሊቀ - ክህሎት ብጽፍበት ነው የሚሻለኝ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   አንድ የወግ ገበታ መፃፍ ያንሰዋል። ይህ ለዘመኑ የምርምር መዕከል የሚያስከፍት #ተቋማዊነት ነው። ይህ በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ #ካሪክለም ተነድፎለት ልጆች ሊማሩት የሚገባ ስኩን የክህሎት ሂደት ነው። ይህ ኢትዮጵያ የተረጋጋ መንፈስ መጠነ ሰፊ ህሊና እና የመቻል አቅም ያላቸው ልጆች እንዳሏት የሚያስነብብ፤ የሚተረጉም፤ የሚያመሳጥር የቅኔ #ቀንዲል ነው።   እንዲህ ዓይነት ስኩን ተግባር ይከውኑ የነበሩ እኔን በቅርበት ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው የቀረጹኝ በዘመነ ኢሠፓ የጓድ ገብረመድህን በርጋ፤ የቺኮዝሎባካያ እና የሃንጋሪ አንባሳደር የነበረው የአንባሳደር ወንድወሰን በዘመኑ የነበሩ የሌሎችም የፖለቲካ ሊቀ- ሊቃውንታት የሙያ ርጉ አባቶቼ የተግባር አምሳያ ነው። ስለሆነም እያንዳንዱን ክፍል ሦስት /// ሦስት ጊዜ አዳምጨዋለሁኝ።   ኢትዮጵያ ህግ ናት። ኢትዮጵያ ፍልስፍና ናት። ኢትዮጵያ ሳይንስ ናት። ኢትዮጵያ ዩንቨርስ ናት። ኢትዮጵያ #ይሉኝታም ናት እያልኩ በድፍረት መፃፍ ከጀመርኩ ወደ ፲፭ ዓመታት ተጠግ...

ኢትዮጵያ ሥመ - ጥር፤ ጀግና ጨዋ የሠራዊት መሪ ነበራት።

ምስል
  ኢትዮጵያ ሥመ - ጥር፤ ጀግና ጨዋ የሠራዊት መሪ ነበራት።    "አቤቱ ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ።" አሜን።    በዘመኔ ያየኋቸው ቆፍጣና፤ ንቁ፤ ትጉህ፤ ዲስፕሊንድ የኢትዮጵያ የሠራዊት መሪወች፤ የሠራዊቱ አባሎች አቋቋማቸው፤ አረማመዳቸው፤ የአነጋገር ዘይቤያቸው #ቁጥብነት ፤ ሥርዓታቸው፤ የአለባበሳቸው ጥራት ፈጽሞ አይረሳኝም።    በእኔ የልጅነት - ዘመን፤ በእኔ የወጣትነት - ዘመን፤ በእኔ የሥራ - ዘመን፤ በእኔ የኃላፊነት እና የተጠያቂነት - ዘመን ያዬኋቸው #ቆፍጣና ፤ #ጥንቁቅ ፤ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ብቻ #መለዮቸው ያደረጉ ድንቆች አይረሱኝም። ኢትዮጵያ ብቃት ያለው ሠራዊት ነበራት። ያው የኢትዮጵያ የችግር ምንጭ የፖለቲካ ኢሊቱ የአመራር ጥበብ ማነስ ይሁን ሌላ ብቻ በጣም ብዙ መስዋዕትነትን የከፈሉ ዕንቁ የጦር መኮንኖች፤ የሠራዊቱ አባላቱም ህወሃት ሥልጣን ሲይዝ በተናቸው። ያ በተመክሮ፤ በዕውቀት፤ በብቃት የሠለጠነ ተቋም በአመዛኙ በህወሃት አማተር ሠራዊት ተተካ። በጫካ ዲስፕሊን ነገሩ ሁሉ ተቀመመ።    የኢትዮጵያ ሊቃናት ስለምን #አድካሚውን መንገድ እንደሚመርጡ ባይገባኝም፤ የትውልዱ ድካም እና ልፋት ባክኖ መቅረቱ ግን በእጅጉ ያንገበግበኛል። በየቤታችን ወንድሞቻችን ገብረናል በናቅፋ በአፋቤት በርሃ።   የሆነ ሆኖ ትልቅ ሰው #አይሞትም ህያው ነው። ክቡርነታቸው ልጆችም ስላላቸውም ተመስገን ነው። እኒህን ታላቅ ሰው ኢትዮጵያ ስታጣ ኢትዮጵያን እግዚአብሄር #ያጽናሽ ማለት ይገባል።   በተጨማሪም ለቤተሰብ፤ ለወዳጅ ዘመድንም መጽናናቱን እመኛለሁኝ። ከእኛ የቀደመው ትውልድ መራራ ስንብት እያደረገ ነው። አይዋ አይለዬ #ሞት ወደ እኛም እየገሰገሰ ነው። ...

A+ #ብራቦ አማራ ክልል። በዘመንህ እንዲህ የልብ አድርስ ተግባር ብየ እምመሰክርልህ አልነበረኽም።

ምስል
  A+ #ብራቦ አማራ ክልል። በዘመንህ እንዲህ የልብ አድርስ ተግባር ብየ እምመሰክርልህ አልነበረኽም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   ምዕራፍ ፲፯     #የማንነት #ቀውስ እና ሙሁርነት #ግብግብ ገጠሙ። "ግዕዝ የሞተ ቋንቋ ነው ዶር በድሉ ዋቅጅራ።" መሃከነ!   አይዋ እከሌ፤ ቢማሩ --- ቢመራመሩ ግዕዝ በአበጃት አገር ላይ ነው። ፈላስፋ ቢሆኑ ሳይንቲስት፤ ኤክስፐርት ቢሆኑ የዩንቨርስቲ መምህር፤ ከመጨረሻው የዕውቀት፤ የሥልጣን መንበር ላይም ቢደረሰም፤ የዘመን ጋሻነትም ቢኖር፤ በመልክ፤ በቁመና የሚያስጎመጁ ዓይነት ሸበላም ቢሆኑም #የማንነት #ቀውስ ካለ የሃሳብህ ክሳትን ቀጫጫነትን እርስወን መዝኖ መዝኖ አደባባይ ላይ #ያሰጣል ።    #ሙጃ ሃሳብ ለትውልድ #የአረም ክርም ነው። የግዕዝ ቋንቋ ቋንቋ ብቻ አይደለም #የሚስጢር ፤ #የፈውስ ፤ #የስኬት #ማህጸን እንጂ። ለእርስወ ይቀራል እንጂ እጬጌው ግዕዝ በግሎባል ደረጃ ከፍ ብሎ ከተቀመጠበት መንበር ንቅንቅ ሊያደርጉት ከቶውንም አይቻልም። #ቁጭላ ሃሳብ ቋት አይገፋምና። በትንታ አጋዢነት በኖ ይቀራል።    ልባሞቹ አገራት፤ ትንግርቶቹ - አህጉራት፤ ሥልጣኔያቸው የተቀመመው በግዕዝ የሚስጥራት ጥልቅ #ልቀት ነው። ለዚህም ነው ቋንቋውን ልጆቻቸው ይማሩት ዘንድ በከፍተኛ ተቋሞቻቸው የተገባውን ደረጃ ሰጥተው እንዲማሩ የሚያደርጉት። የአጤ ጀርመን የመዳህኒት ቅመማ ከኢትዮጵያዊው የፈውስ መጸሐፍ ልቅናም ይቀዳል። የራሳቸውን የሚያከብሩት ጀርመኖች፤ የዕውቀት ዘርፍን በድንበር ወይንም በዞግ ሳይከልሉ ነፃነቱን ዓውጀውለታል። ይባረኩ። አሜን።   ማህበረ አያ እከሌወቼ የተፈጠሩበትን ዝሃ - ግራ፤ የተገኙበትን የእ...