ልጥፎች

ከጃንዩወሪ, 2020 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ዱዳው የአብይዝም የኦሮሙማ ሌጋሲ አናባቢ አልቦሽ ነው፤ ሰደከበተ SDKBT።

ምስል
እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ። ዱዳው የአብይዝም የኦሮሙማ ሌጋሲ አናባቢ አልቦሽ ነው፤ ሰደከበተ SDKBT። „ አቤቱ ሰውነቶቼን ለአንተ ሰጠሁ።“ (መጽሐፈ ጦቢት ምዕራፍ 3 ቁጥር 12) ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 31.01.2020 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·         በር። እንዴት ናችሁ ቅኖቹ የአገሬ ልጆች? እርህርህና የኦሮሙማን የዴሞግራፊ ጭካኔ ተረከብ እዬተባለ ነው። የዛሬው እርስ ጉዳዬ ይህ ነው። መቼም ይህ ዘመን መልካሙን ነገርን አሳዬን ብለን ማሰብ ያለብን ይመስለኛል። ፈተናው በራሱ ኢትዮጵያ በማን ውስጥ እንደ ተሰናበተች እዬተሰተዋልን ነው። ቀድሞውንም እሷ በውስጡ የሌለችበት ነፍስ ሁሉ ሲምል ሲገዘት ዕድሜውን የሸኜበት፤ ትልሙም መክኖ ሲፈርስ ሲሰራ የተኖረበት፤ የውስጥ የክህደቱ የውድቀት ስምጥ ሸለቆም ኮለል ብሎ የታዬበት ዘመን ነው። ያልወደቀ፤ ያልተንከባለለ፤ ያላዳጠው፤ ያልተነኳኮተ ማግኘት አይቻልም። ብልሁ ኢትዮጵያዊነት ማጣሪያ ወንፊቱ በመዳፉ ነውና።   ዘመኑ ይመስገን ኢትዮጵያዊነት የታደመባት፣ አገር ኢትዮጵያ ተጠምዳ የተያዘችበት በማን መዳፍ ሥር እንደወደቀች፤ እንዴትም እንደሚነግድባትም፤ በጥርስ የተያዘችበት ሁኔታም በአስተውሎት ፍንትው ብሎ ያዬንበት ወቅትም ነው። ከዚህም በተጨማሪ ማን ለቃሉ እንደ አደረ፤ ማን ደግሞ ቃል አባይ እንደ ሆን፤ ማን ደግሞ ከሞቀው ዘፋኝ እንደ ሆነ፤ ማን አሸብሻቢ እንደሆነ እያዬን ነው። ስለዚህ ዘመኑን ባገኘው የአንገት ሃብል አስርለት ነበር። እኔው። እንደ ጉድ ነው የተንተረተረው የህሊናው አቅም ሁሉ። ሲመከርባት፤ ሲዶለትባት የኖረችው ቅኒት ኢትዮጵያ ገመናውን ሁሉ አያዬችው ነው። ታዘበችው። ጡቷን አሽ