ልጥፎች

ከዲሴምበር 25, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

መንትዮሾቹ ከቁልቋል አጫዋችነት ወደ ኦዳ አራጋቢነት የተገለበጡት ልብጣዊ ነፍሶች።

ምስል
እ ንኳን ወደ ቀ ንበጥ ብ ሎግ በ ሰላም መ ጡልኝ። „ፊታቸውን ሳይሆን ጀርባቸውን   ሰጡኝ፣ በመከራቸው ጊዜ ግን ተነስተህ አድነን ይላሉ።“   ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፳፯ መ ንትዮሾቹ ከቁልቋል አ ጫዋችነት ወደ ኦዳ አራጋቢነት የተገለበጡት ልብጣዊ ነ ፍሶች። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·     እ ፍታ የሰማዩ አሻቦ ሲጠበቅ ትውር ሳይል በደመና ተደሞ የዓውደ ዓመቱ ሥርዓቱ እዬተፈጠመ ነው። ነፍስ ተ - እንቅስቃሴ የተገደበ ይመስላል። ጸጥ - ረጭታ እንደ ቤተ መቃብር ሆኗል። የቤቴ እርግቦች እራሱ እሱ አፋቸውን   የተባሉ ይመስል ኮሽታ የላቸውም። ድምጥም የለም። ብቻ እርጋታ በ - ጫታ ሰፍኗል- ዕለቱ። ግርማ ሞገሱ ግን ያስፈራል። ጭሯቸው ብቻ የተንጫረረው ግንዶኢን ባልስ ዳንስ ላይ ይገኛሉ፤ እቴጌዋ ከመንበሯ ብቅ ብላ አፈር እንደ ማለት አሰኝቷት ከንፈሯን ነፋ አድርጋ ሽው ትላለች። እንዴት ናችሁ የኔዎቹ ቅኔዎቹ የአገሬ ውዶች? ዕለቱን ባዕላችን ብላችሁ ለምታከብሩት ሁሉ መልካም የስኬት ዓውድ ዓመት አንዲሆንላችሁ እመኛለሁኝ። ትህትና ይታከልበታል። የ ወግ ገበታ። ዛሬ ስለ ግልብጥ ሲብሊንገኖችን ትንሽ ነገር መቋጠር ፈለግሁኝ። ለነገሩ እኛንም ገልብጠው ጋልበውናል - የዛሬን አያድርገው እና። ሁለቱም ሥም የለሾች ናቸው - ተዛሬ ላይ። ሥም የለሽነታቸው የሚያውቀው የቁልቋል አምላክ እና የኦዳ አምላክ ብቻ ናቸው። ግን ልበ - ጥፉን በሥም ይደግፉ እንዲሉ እነዛ ቅን፣ ደግ እና ቸር ወላጆች ምን የመሰለ ድንቅ ሥም አውጥተውላቸው ነበር። ልጅ ደመቀ መኮነን እና ልጅ ገዱ አንድርጋቸው ብለው። ነገር ግን ነፍስ አውቀው ፖለቲከኛ ከሆኑ ጀምረው የወላጆቻቸውን ሥጦታ