ልጥፎች

ከዲሴምበር 9, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ነፃነት ቅኔ ነው!

ምስል
ነፃነት ቅኔ ነው! "በእውነት ጥበበኛ ሰው ራሱን ይጠቅማልን?" መጽሐፈ እዮብ ፳፩ ቁጥር ፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute© Selassie  16.06.2013 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። እንዴት ናችሁ ክብረቶቼ ይህም የ2013 ጡሑፍ ነው። ፡ እሜቴ ነፃነት እንድምን ይዞሻል? እንዴትስ ከርመሻል? ከእመናው ሸክማ ሸክምሽ ዘንድሮስ ከብዶሻል እልፈት የለው ኑሮሽ እንዲህ ይፈትልሻል። ተርጓሚ ሲገኝ ነፃነት ቅኔ ነው። ነፃነት ረቂቅ ጥልቅ የተባረከ የመንፈስ ውስጥ ፍላጎት ነው። ነፃነት የሰለጠነ ህዝብ ብቸኛ የግናዘቤ መለኪያ ነው። ነፃነት ሰፊ የሰብዕዊነት ማሳ ነው። ነፃነት የሃይማኖት መሰረታዊ ቃል ነው። ነፃነት በጥሬው ብቻ ሊተረጎም የማይችል ውስጥን በራስነት የማናፅ ሥልጡን ክስተት ነው። ነፃነት ዛሬ የዓለማችን ጉልተ - አጀንዳ ነው። ነፃነት ዛሬ የዓለምን መንፈስ በአንድ ሃዲድ ያገናኘ ቅዱስ አምክንዮ ነው። ነፃነት ህይወት ላላቸው ብቻ ሳይሆን ለግዑዛን ሳይቀር ተቆርቋሪ ጠበቃ ነው። ይህችን ትንሽ ዘርዘር ባደርጋት መልካም ነው ከተጠቀለለች እንዳትጠጥር … በመጠኑ ስለምን ነፃነት ለግዑዛን ሳይቀር አስትንፋስ ሆነ?  ምክንያቱም ግዑዛኑም ቢሆኖ በሰው ልጅ ታሪካዊ ሂደቶች ብቁ ታዳሚ ከመሆናቸው በላይ ትናንትን ለዛሬ - ዛሬን ለነገ፤ ነገን ለነገ ተወዲያ ያቀባባሉ፤ ያሰብላሉም  ባለውለታዎቻችን ናቸውና፤ አሁን የዋሻ ዘመናት ታሪክ በድንጋይ ላይ ተቀርጸው ይገኛሉ። ብዙም ይናገራሉ፤ መሬት በከርሷ እፍን ሽክፍ አድርጋ ያያዘቻቸው ቅሬተ - አካላት ትናትን አበክረው ያውጃሉ፤ ከመነሻም ይገነባሉ። ለዝንተ ዓለም ዝክረ ንዑዳን ናቸው። ለዛሬ ሥልጣኔም የምርምር ማዕከል እኮ የትናት ትንግርት ክንውን ነው። ክን

ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው...

ምስል
ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው ጊዜ እሲኪሰጣቸው ድረስ ጠብቀው ይይዙት ዘንድ  እለምናቸዋለሁ። "አለመታገሥ ስለምን አይገባኝም?"  መጽሐፈ እዮብ  ፳፩ ቁጥር ፬     ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ 23.12.2013 ·        መግቢያ። አሁን ሳስበው እኔ እና ሳምንበትም ጊዜ ሰጥቷናል እላለሁኝ። ግን እንዴት ናችሁ የኔዎቹ። ይህ ብሎግ ሥራ የጀመረው በግንቦት 1 ቀን በ2018 ነው። ከዚህ ቀደም በስፋት የተሠሩባቸው ጉዳዮች በዘሃበሻ ወይንም በኢትዮ ርጅሰተር ነው። ቀደም ባለው ጊዜ በራሴ በጸጋዬ ድህረ ገጽ እና ራዲዮም ነው። እኛ እራሳችን ሲሞላብን እንደምንቀንሰው ሁሉ ዘሃበሻም ሆነ ኢትዮ ሪጅሰተር ሆነ ዘሃበሻ እነሱ ደግሞ አርኬቡ ሲሞላባቸው መቀነስ ግድ ይላቸዋል። ግሎባል ጉዳዮችን ስለሚያስተናግዱ ጫና ይበዛባቸዋልና።   ስለዚህም ጹሑፎቼ ሊሠወሩ ይችላሉ። ታሪክ ነው። ታሪኩ የኢትዮጵያ የነጻነት ትግል በአንዲት ዜጋ ዕይታ እንደ ዘመኑ ነው። ዛሬ በ2013 እንደምጸፈው ዛሬ አልጽፍም። ስለምን? ዘመኑ በራሱ የሚያመጣው ለውጥ ስላለው።  ግን በዛ ዘመን የነበረው ዕይታ እና ግንዛቤ ዛሬን በሃሳብ በማገናኘት እረገድ ምን ድርሻ አበርክቷል የሚለውን ያሳያል፤ በሌላ በኩል ግን የአንባቢያን ዕይታም በዛ ዘመን በነበረው ንቃተ ህሊና ልክ የተሠራ ስለመሆኑ ልብ ሊለው ይገባል። ስለሆነም ከጻፍኳቸው ወዘተረፈ ወጎች ውስጥ በዚህ ብሎግ እንዲቀመጡልኝ የምፈቅዳቸውን በተከታታይ ፖስት ለማድረግ አስባለሁኝ። www.tsegaye.ethio.info ያለው እንደ ተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው። እንዲህ ነበር የተጀመረው በ2014 ·        በሴቶች ስሜት ውስጥ መሆንና በስሜቱ ውስጥ ሴቶችን ሆ

ለዝክንትለኛዋ ዓለም ፈውስ ትሆን ዘንድ የተመረቀች - የተመረጠች - ሴት!

ምስል
መኖር እንዲያምርበት …. „ልቤ በመናፍቅ ዝሏል።“ መጽሐፈ እዮብ ፲፱ ቁጥር ፳፯ ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selasssie 09.02.2014 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ -ዙሪክ) ·        መግቢያ። እንዴት ናችሁ የኔዎቹ። ይህ ብሎግ ሥራ የጀመረው በግንቦት 1 ቀን በ2018 ነው። ከዚህ ቀደም በስፋት የተሠሩባቸው ጉዳዮች በዘሃበሻ ወይንም በኢትዮ ርጅሰተር ነው። ቀደም ባለው ጊዜ በራሴ በጸጋዬ ድህረ ገጽ እና ራዲዮም ነው። እኛ እራሳችን ሲሞላብን እንደምንቀንሰው ሁሉ ዘሃበሻም ሆነ ኢትዮ ሪጅሰተር ሆነ ዘሃበሻ እነሱ ደግሞ አርኬቡ ሲሞላባቸው መቀነስ ግድ ይላቸዋል። ግሎባል ጉዳዮችን ስለሚያስተናግዱ ጫና ይበዛባቸዋልና።   ስለዚህም ጹሑፎቼ ሊሠወሩ ይችላሉ። ታሪክ ነው። ታሪኩ የኢትዮጵያ የነጻነት ትግል በአንዲት ዜጋ ዕይታ እንደ ዘመኑ ነው። ዛሬ በ2014 እንደምጸፈው ዛሬ አልጽፍም። ስለምን? ዘመኑ በራሱ የሚያመጣው ለውጥ ስላለው።  ግን በዛ ዘመን የነበረው ዕይታ እና ግንዛቤ ዛሬን በሃሳብ በማገናኘት እረገድ ምን ድርሻ አበርክቷል የሚለውን ያሳያል፤ በሌላ በኩል ግን የአንባቢያን ዕይታም በዛ ዘመን በነበረው ንቃተ ህሊና ልክ የተሠራ ስለመሆኑ ልብ ሊለው ይገባል። ስለሆነም ከጻፍኳቸው ወዘተረፈ ወጎች ውስጥ በዚህ ብሎግ እንዲቀመጡልኝ የምፈቅዳቸውን በተከታታይ ፖስት ለማድረግ አስባለሁኝ። www.tsegaye.ethio.info ያለው እንደ ተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው። ·        እንዲህ ነበር የተጀመረው በ2014 ጡሑፈ … አዳም እንደተቆለፈ ነው …. ለገርገብም .. እእ - ግን አዳም እንዴት ነበር ለህያውን ዕውቅና የሰጠው እንደ መሰጠረው አለፈ ማለት ነው …. አዋቂ ነገር ዬት ይገኝ ህም! ያለፈው ሰ

እናት አድማጮቿን አክብሪ ናት፤ ትናንትን በምለሰት ዛሬን በጨረፍታ ...

ምስል
አቅምን የማደራጀት ክህሎት - ከሴቶች ተፈጥሮ ይቀዳል። (የ20014 ዓለም አቅፍ የሴቶችን  ቀን ታስቦ የተዘጋጀ።) „እንግዲህ እነዚህን ቃሎች በልባችሁና በነፍሳችሁ አኑሩ፤  እነርሱንም ለምልክት በእጃችሁ ላይ እሰሯቸው፤ በዓይኖቻችሁም መካከል እንደ ክታብ ይሁኑ።“ ኦሪት ዘገዳግም ምዕራፍ ፲፩ ቁጥር ፲፰   ከሥርጉተ©ሥላሴ (Sergute©Selassie) 08.03.2014 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ) ·        መግቢያ። እንዴት ናችሁ የኔዎቹ። ይህ ብሎግ ሥራ የጀመረው በግንቦት 1 ቀን በ2018 ነው። ከዚህ ቀደም በስፋት የተሠሩባቸው ጉዳዮች በዘሃበሻ ወይንም በኢትዮ ርጅሰተር ነው ያሉት። ቀደም ባለው ጊዜ በራሴ በጸጋዬ ድህረ ገጽ እና ራዲዮም ነው። እኛ እራሳችን ሲሞላብን እንደምንቀንሰው ሁሉ ዘሃበሻም ሆነ ኢትዮ ሪጅሰተር እነሱ ደግሞ አርኬቡ ሲሞላባቸው መቀነስ ግድ ይላቸዋል። ግሎባል ጉዳዮችን ስለሚያስተናግዱ ጫና ይበዛባቸዋልና።   ስለዚህም ጹሑፎቼ ሊሠወሩ ይችላሉ። ታሪክ ነው። ታሪኩ የኢትዮጵያ የነጻነት ትግል በአንዲት ዜጋ ዕይታ እንደ ዘመኑ ነው። ዛሬ በ2014 እንደምጸፈው አልጽፍም። ስለምን? ዘመኑ በራሱ የሚያመጣው ለውጥ ስላለው።  ግን በዛ ዘመን የነበረው ዕይታ እና ግንዛቤ ዛሬን በሃሳብ በማገናኘት እረገድ ምን ድርሻ አበርክቷል የሚለውን ያሳያል፤ በሌላ በኩል ግን የአንባቢያን ዕይታም በዛ ዘመን በነበረው ንቃተ ህሊና ልክ የተሠራ ስለመሆኑ ልብ ሊለው ይገባል። ስለሆነም ከጻፍኳቸው ወዘተረፈ ወጎች ውስጥ በዚህ ብሎግ እንዲቀመጡልኝ የምፈቅዳቸውን በተከታታይ ፖስት ለማድረግ አስባለሁኝ።  www.tsegaye.ethio.info ያለው እንደ ተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው። በዚህ ጹሑፍ መግቢያ ላይ