ልጥፎች

ከኤፕሪል 11, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አላልቅአለኝ ህምታ!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ    አላልቅአለኝ ህምታ! „ለሁሉም ዘመን አለው። ከሰማይ በታችም ለሆነው ነገር ሁሉ ጊዜ አለው። ለመወለድም ጊዜ አለው። ለመሞትም ጊዜ አለው፤ የተተከለውንም ለመንቀል ጊዜ አለው፤ ለመግደል ጊዜ አለው፤ ለመፈወስም ጊዜ አለው፤ ለማፈረስም ጊዜ አለው፤ ለመሥራትም ጊዜ አለው፤ ለማልቀስም ጊዜ አለው“ መጽሐፈ መክብብ ምዕራፍ ፫ ከቁጥር ፩ እስከ ፫                                     "እኔም ተመለስኩ ከፀሐይ በታች የሚደረገውን ግፍ ሁሉ አዬሁ፤                                      እንሆም የተገፉት ሰዎች እንባ ነበር የሚያጽናናቸውም አልነበረም                                     በሚገፏቸው እጅ ሃይል ነበር ፤ እንርሱን ግን የሚያጽናናቸው አልነበረም ።                                      እኔም እስከዛሬ ድረስ በሕይውት ካሉት ይልቅ በቀድሞ ዘመን የሞቱትን                                     አመሰገንሁ ከእነዚህም ከሁለቱ ይልቅ ገና ያልተወለደው ከጸሐይም                                      በታች የሚደረገውን ግፍ ያላዬው ይሻላል። " መክብብ  ፬ ከቁ ፩ -፫                                                                          አላልቅአለኝ            ጥምልምሉ            አላልቅአለኝ ጥምንምኑ አላልቅአለኝ             ጥልፍልፉ            አላልቅአለኝ ጥምዝምዙ            አላልቅአለኝ ንጥፍጥፉ አላልቅአለኝ             

አማራጭ የለም… ስለምን?

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ                 አማራጭ       የለም…               ስለምን? „ዮሴፍም እርስ በርሳቸው የደኅንነትና የፍቅር  አሳብ እንዳላቸው የጠብም  አሳብ እንዳላቸው  አሳባቸውን በሚያውቅ ገንዘብ አሳብን አሰበ።“ መፅሐፈ ኩፋሌ ፴ ቊጥር ፩  ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 11.04.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። ይህ ተጋድሎም ለኦነግ እንዳወጣ ተቸብችቧል። ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? ውይ ዛሬ ከፍቶታል። ዛሬ ካፌዋን ጨለጥ አላደረገም መሰል። ጭፍግግ ብሎ ነበር መስኮቴን ስከፍተው የጠበቀኝ። ተዚህ እንዲህ ከሆነ አላዛሯስ ኢትዮጵያ ማለቴ አልቀረም… ያው  በአለችየለችም እዬተናጠች ነው … ይመስለኛል። እኔ ፈሪ ከሆንኩኝ ሰነባብቻለሁኝ። መፍራት ሲያንስ ነው?   አቅጣጫ የለሹ ጦሮ እያስነካን ነው በጅዋጅዊት … መጥኒ እኛን ለፈጠረች እትብት። በዬዘመኑ አምልኮተ ነገራችን የጣዖታችን መበረከቱ … አይጣል ነው። አንድን ድርጅት ወይንም አንድን ግለሰብ መውደድ፤ ማክበር፤ ማድነቅ፤ መደገፍ መብት ነው። መንቀፍም ሰብዕናን እስካልተዳፈረ ድርስ እሴታዊ ትሩፋቶችን እስከ አለገነጣጠልነው ድረስ የተገባ ነው። ይህ በግለሰብ ደረጃ ነው። እስከ አሁን በኖርንበት ዘመን በማከብር፤ በማድነቅ እና በመቃወም፤ እንዲሁም በመውቀስ ጉዳይ ላይ መብት መሆኑ ቀርቶ የጦርነት ቀጠና ሆኗ ነው የኖረው 50 ዓመት ሙሉ። በቃ ሰብሰብ ማለት አውሊያችን አይወድለትም። ጥሎብን መካሳስ እና መገፈታተር ነው ስክነታችን … „አያጣልን ያቀላል ሰው“ አለች እሚታ ጽግሽ ...  … አሁን ከዚያ ሸጎሪያም ቅርቃር ዘመን ወጥተን ተፈጥሯዊና ሰዋዊ መንፈስ ይሰፍናል