ልጥፎች

ከኦክቶበር 1, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የብአዴን የሥም ለውጥ የተስፋ ልጣጭ ነው።

ምስል
የሥም መዋጮ ተስፋ ሙጣጭ - ልጣጭ። „እንሆ በማትረቡበት በሃሰት ቃል ታምናችኋዋል።“ ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፯ ቁጥር ፰ ከሥርጉተ© ሥላሴ 01.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። መሆን መቻል እና መሆን መፈለግ ልዩነት አላቸው።  የባህርዳሩ  የአማራን ሥም የተሸከመው የብአዴን ጉባኤ ደንቡ ላይ የ አባልነትን መስፈረት በሚመለከት ለውጥ እንደሌለው ገልጾልናል። "ደንቡን እና ፕሮራሙን የተቀበለ ማንኛውም ዜጋ አባል መሆን ይችላል፤ መሪ መሆን ይችላል ብሎናል።" የዶር አንባቸው እና የዶር ገዱ አንዳራጋቸው የወጣቶችን ባህርዳር ወሎ ደብረታቦር ያነጋገሩበት፤ ያወያዩበት ድካማቸው አሳዘነኝ። የውነት አሳዘነኝ። የውርንጫ ድካም ነው። ለዚህ ፌክ ጉዞ ከመድከም በዝምታ መታደም በስንት ጣዕሙ። ስለዚህ ጉዳይ ከሆነ ስለምን ጊዚያቸውን ያባክናሉ? ይህችን መሰል ተረብ አደማ ላይ፤ ትግራይ ላይ፤ አሶሳ ላይ፤ አፋር ላይ፤ ቤንሻንጉል ላይ አትሞከርም። ማላጋጥ!  የአማራ ዴሞክራሲያ ፓርቲ መባል ሥሙ ምን ያድርገለታል - ለአማራ። ዓርማውም ቢሆን አባይ የኢትዮጵያ ሃብት ነው። አማራነት  በማለት ሳይሆን በመሆን ሆኖ መገኘትን ይጠይቃል። ከኢህአዴግ ጉባኤ የመጨረሻ ወሳኔ በኋዋላ በጠ/ ሚር አብይ አህመድ ቀጣይነት ላይ ተ ጽዕኖ ማሳደር ስላማልፈግል አንጠልጥዬ በቀጠሮ ዋናውን ፍሬ ነገር አሰነብተዋለሁኝ።  በጣም ሞጋች ጉዳዮች ይነሳሉ ዘግዬት ብለው። አሁን ግን አሳቸው እንዲቀጥሉ ስለምፈልግ በዝምታ መቆዬትን እምርጣለሁኝ። የሆነ ሆኖ ትናንት የወያኔ ሃርነት ግርፍ የነበረው ብአዴን ሥሜን ቀዬርኩ ይለናል። ድሮም እኮ በአማራ ውስጥ አልነበራችሁም። አሁንም የላችሁም። ወዲፍትም አትኖሩም።  ተልዕኮችሁ ምን ስለመሆኑ አሳምረን እናው

የተጋመድንበት ፈትል

ምስል
የተጋመድንበት ፈትል።   „ጥበብስ በቀደሙ ሰዎች ሁሉ ዘንድ ተመረመረች።     መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፱ ቁጥር ፩“ ከፋሲካ © መለሰ   ተሾመ መስከረም 2011 ዓ . ም አባታችን ወደ አስራ ሶስት ልጆች ነበሩት፡፡ ከተለያዩ ሴቶች፡፡   ዘር ቆጠራ ባልችልበትም፣ የአባቴ ሚስቶች ስብጥር ከአማራ፣ ከኦሮሞ፣ ከጉራጌ፣ ከትግራይ እና ከኤርትራ ነው፡፡ እድለኛ ስለኾንኩ ከአንዷ በስተቀር ከኹሉም ከአባቴ ሚስቶቼ ጋር አብሬ ኖሬአለኹ፡፡ እናቴ ከአማርኛ ተናጋሪ ቤተሰብ ነው የመጣችው፡፡   ኾኖም በህጻንነቷ ወለጋ እና ኢሉባቦር አድጋለች፤ ስለዚህ ኦሮምኛ አቀላጥፋ ትናገራለች፡፡ በጣም ተናዳ ሰው መገሰጽ ስትፈልግ ወይም ንግግሯን በተረት ማሳለጥ ሲያሰኛት የምትጠቀመው በኦሮምኛ ነው፡፡ አ ሁ ን ሳስበው ኦሮምኛ የሚናፍቃት ይመስለኛል፡፡ አማራኛ እና ኦሮምኛ የሚናገር ሰው ካገኘች ኦሮምኛውን ትመርጣለች፡፡ በአኹኑ ዘመን አራዳዎች አነጋገር ኦሮምኛ ውስጧ ነው፡፡ ልጆቿን ያሳደገችን የአማራን ባህልና ስነልቦና ከኦሮሞው ጋር አጋምዳ እና ፈትላ ነው፡፡ ሌላዋ ያባቴ ሚስት ጉራግኛ ተናጋሪ የሆነችው ነጋዴዋ እትየ ዘነቡ ነች፡፡ ካባቴ ጋር ከተፈታችም በኋላ ቢኾን ከቤቷ አልጠፋም ነበር፡፡ በኹለት ምክንያት፤ በመጀመሪያ ኹለት ወንድሞቼን እና አንዷን እህቴን የወለደችው ካባቴ ስለሆነ፣ ኹለተኛው ደሞ የምንኖረው ባንድ ቀበሌ ነበር - የመርካቶው መሳለሚያ እና ኳስ ሜዳ፡፡   አባቴ ያንን ሰፈር እስከለቀቀ ድረስ በተለይ ቅዳሜ እ