ልጥፎች

የአላዛሯ ኢትዮጵያ ድንብልብል መከራ፡

ምስል
ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ። „ታላቅ ክንፍ እና ብዙ ላባም ያለው ሌላ ታላቅ ንስር ነበር፤ እነሆም ያጠጣው ዘንድ ይህ ወይን ሥሩን ወደ እርሱ አዘነበለ አረጉንም ከተተከለበት ከመደቡ ወደ እርሱ ሰደደ።“ ትንቢት ህዝቅኤል ፲፯ ቁጥር ፯ እስከ ፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 01.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·       የገማናችን ብርከታው።   ይግርም ነው። አቶ ጌታቸው አሳፋ ሱዳን ሄዱ የሚለው ነገር አያሳምነኝም እዛው ትግራይ ውስጥ ነው ያሉት ብዬ ጽፌ ነበር፤ አይደለምን? አሁን ይድነቃችሁ ብለው የወያኔ ሃርነት ትግራይ የምክር ቤት አባል ሆነው መመረጣቸው ብቻ ሳይሆን በቀጣዩ የኢህአዴግ ጉባኤም እንደሚታደሙም ተገልጧል። የማስፈራሪያ ትልቁ ዘንግ፤ የማንአለብኝነትም ተጋድሎ …    ለዚህም ነበር እኔ ችግሩ ሌቦች ተፈቱ ሳይሆን ለውጡ ሊቀለበስ ይችላል ብላችሁ እሰቡ ያልኩት" ጭንቁ ሌቦች አቅም አገኙ ነው "    ፤ አቅማቸውን አጠናከረው የወያኔ ሃርነት ትግራይ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወይንም ሞት ብለው ተነስተዋል። እኛም ጉዝጓዝ ሆነን መባጀታችን መርሳት የለብንም።  ኦዴፓ ውስጥም ማን ማንን እንደሚደግፍ አዲስ እጩ ያቅርቡ አያቅርቡ ገና ሰው ልብ ያላለው ጉዳይ ነው። ኦዴፓ ሙሉ ድምጹን ይዞ ይጋባል የሚል ዕድምታ አነባለሁኝ። ከሆነ ጥሩ ነው።  ነገር ግን የአቶ ጃዋር መንፈስ ሌላ መሰናዶ የለውም ብሎ ማሰብ እራስን መርሳት ይመስለኛል። ሌላ ድልድይ ፈላጊዎች ናቸው። አፈንግጦ ለመውጣትም የተሰናዱበትን አመክንዮ ሊኖር ስለ መቻሉም ፈጣሪ ነው የሚያውቀው። ያ ባይሆን ወያኔ ሃርነት ትግራይ ይህን ያህል የልብ ልብ አያገኝም ነበር።  ሌላው ወሳኙ የደቡብ ህዝቦች ፓርቲ ነው። ስበሰባው አላለቀም ምን የት ላ

ከመጋቢት 24 ጀምሮ የተጠለፈው የሴራ ጉንጉኑ ሊፈታ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል

ምስል
የወለም ዘለም ዘለበት የተስፋ መባቻ ክስመት። „የማይታዬው፤ ከዚህ የሚበልጠው ፍጥረቱ ግን ጥቂት ብቻ ነው።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፵፫ ቁጥር ፴፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ 30.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ዛሬም እዛው አቶ ጃዋር መሃመድ ሰሞነኛ መግለጫ ሁለቱን ብቻ አነሳለሁኝ። እርግጥ ተያያዥ ሁኔታዎችን ማንሳት ግድ ይላል። የተለመደው የጭንቅ ጊዜ ዓመት ድገሙ እያለን ስለሆነ። መጋቢት ደግሞ ተመልሶ በወርሃ መሰከረም ዱብ ብሎ ጭንቀትን ያስኮተኩተናል።  ስለምን በሰሞናቱ ነገር ምነው ዝምታ ተብያለሁኝ። የኦሮሞ 5 ድርጅቶች ሚዲያቸው እና ተከሳሹ ኢሳት እስከ ግንቦት7 ያለውን ሙግት ሁለቱም በአካል መሬት ላይ ስላሉ ተከታዮቻቸውም ሙሉ ስለሆኑ እንደ ቀደመው ጊዜ ተጠቃ የምለውን ወገኜ ሙግቱ ይብቃኝ ስላልኩኝ ነው። አዬሁት እስኪበቃኝ። ሁሉም ለወገኑ እንጂ እንደ እኔ ያለው ተማላ ገብቶ ከሳት መረመጥ ከምንም የማይቆጠር እንዲያውም በተደጋፊው አቅም ልክ ደጋፊውን በዘመቻ የሚያጠቃ ስለመሆኑ ተማርኩበት። እንኳንስ ደጋፊን ዕውቅና ሰጥቶ ማገዝ ቀርቶበት ሌላ የማጥቃት ዘመቻው ቢቀር በስንት ጣዕሙ። ለዚህ ብልሁ ወያኔ ብቻ ነው። ደጋፊዎችን ጥሎ አይጥልም። ስለመሆኑም ዝምታ በስንት ጣዕሙ በሚል መነካካት አልሻም። የኢትዮጵያ ፖለቲካ አምስግኑኝ እንጂ ውቀሰኙ ብሎ ፈቅዶ አያውቅም። ተመስግኖም አመስጋኙን ሲያጠቃ ነው የኖረው። ወደፊትም ጉዞው እንደዛው ነው። ·        ሁለት ሀሳቦች ይነሱ። በዚህ በሰሞናቱ የአቶ ጃዋር መሃመድ መግለጫ የዶር አብይ አህመድ ሙሉ ደጋፊ እንዲያውም ተሟጋች እና ተቆርቋሪ ሆኖ ቀርቧል። የለውጡም ሐዋርያ እና ለውጡን በማስቀጠል እንደሚታገም ገልፆልናልን። ለውጡ በማን ከተመራ ይሆን እሱ የሚደገፈ