ልጥፎች

ከፌብሩወሪ 22, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

? የመጨረሻው ዳርቻ የት ነው?!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ? የመጨረሻው ዳርቻ የት ነው?! „አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ?“ መዝሙረ ዳዊት ፳፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 22.02.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። አሁን አንድ ዜና ሰማሁኝ። ዶር ለማ መገርሳ የለገጣፋው መፈናቀል እንዲቆም ማዘዛቸውናን እና ከህዝቡ ጋር ለመነጋገር መፍቀዳቸውን። እንግዲህ ነፍሰ ጃውርውያን አቶ ንጉሹ ጥላሁን እና አቶ አዲሱ አረጋ አነ ሰውር ሐዋርያቱ ከጎበኙ በኋዋላ የተሰጠ ተስፋ መሆኑ ነው።   ዜናው ዕውነት ከሆነ መልካም ነው። እኔ ግን መጨረሻው ፍርጥርጥ ብሎ መታወቅ አለበት ባይ ነኝ። ብልጥ  የኦሮሞ አክቲቢስቶች ቀስ ብሎ መከወን ነበር እያሉን ነው። ይህ ማለት ሙሉ ለሙሉ መደላደል ከተረጋገጠ በሆዋላ እንደማለት ነው። ያን ጊዜ 5ቱ የኦሮሞ ድርጅቶች መግለጫ ሲያወጡ ያሉትን ነው የደገሙት አሁን መሆን አልነበረበትም ብለውን ነበር። መቻል እኮ መቻል ከተሰጠው ባለመክሊት ብቻ ነው የሚገኘው … እውነት ደግሞ ቀን አይቀጠርለትም ለውጡን እንመራለሁ የሚለው ቲም ለማ ኢትዮጵያዊ ለውጥ ወይንስ የኦሮሞ ኢንፓዬር ለመገንባት ነው እዬተጓዘ ያለው? ይህ በፈጣጣው በግልጥ መንገድ ሊገለጥ ይገባል። ልክ ያጣ ነገር እኮ ነው እዬታየ ያለው። ቲም ጃዋር እኮ ስለመምራቱ ምንም አያጠራጥርም። ራስ እግሩ እኮ ህዝብ የሚያሸብር እና ስጋትን ያዘመተ ድርጊት ነው እዬተፈጸመ ያለው። ፋታ ጠፋ እኮ? ለዛውም ጉድጓዱን ህወሃትን አስቀምጦ። የሚገርመው አገር ጠቅልለው የገቡት የቆረበ ሰው ይመስል አፋቸውን ዘግተው በተረታው መስመር የተሰጣቸውን ብቻ እዬከወኑ ይገኛሉ። ድንቅ ያለኝ ደግሞ ስንት ጊዜ በሚበላው የኮሚሽን አባልነቱኝ እሰዬው ብለው መቀበላቸው

የስውሩ መንግሥት ዘመንተኞቹ በለገጣፎ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የስውሩ መንግሥት ዘመንተኞቹ በለገጣፎ። „ ምንም እንኳን በለስም ባታፈራ፣ በወይን ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፣   የወይራ ሥራ ቢጓል እርሾችም መብልን ባይሰጡ በጎችም ከበረት ቢጠፉ ላሞችም በጋጥ ውስጥ ባይገኙ   እኔ ግን በ እግዚአብሄር ደስ ይለኛል፤ በመዳህኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ። “ ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯ ቁጥር ፲፰ የተባረከ አሜን ለተባረከ ትውልድ! ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። የለውጡ ስውር ውጋት! ·        መነ ሻ።  https://www.youtube.com/watch?v=WurKLDQ_GoA አቶ ንጉሱ ጥላሁንና አቶ አዲሱ አረጋ በለገጣፎ ጉብኝት አደረጉ እኔም ያልኩት እኮ ይኸው ነው። አጃን ነው የወቅቱ መሪ ነው ያልኩት። የመንፈስ ጠላፊዎቹ እነሱ ናቸው። ከዚህም ላለፈ ጉዳይ ቢያስኬድ ይቻላል። ቀድሞ መገፋት ያለበት ተገፍትሯል። ጠርጣሬ እንደሆነ አፈር ሆኗል እንደ ወጣ ቀርቷል። ሌላም ቀጣይ ይኖራል። ባለቤት የሌለው ህዝብ እዬሸኙ ዝም።  የሆነ ሆኖ ዛሬ ፋና እንደዘገበው „ ጃ“ ሲቀር „አ“ እና „ን“ ተገኝተው ጉብኝት አድርገዋል ይላል ፋና ከሰቆቃው ውቅያኖስ ጨላልፎ። ይህን ነገር እጅግ በቀደመ ሁኔታ ተቸክችኳል። አድማጭ የለም እንጂ። የህፃናት የሰቆቃ ዕንባ የናፈቀው፤ የእናቶች የማህጸን ደም ዕንባ  ለሚያሰኘው ይህ እርካታ ነው። ጉዳዩ እና ዓላማው በዚህ መከራ ውስጥ በዚህ ጨለማ ውስጥ መከራን እዬመነዘሩ ፌስታ ነውና። የኢትዮጵያ የመፍትሄ ቁልፍ ያለው ከዚህ የጭካኔ የአራዊትነት ውስጥ ነው ልብ ከተገኜ።