ልጥፎች

አዝነን አዝነን እኛም ገርጥተን ሀዘን ሆነን አረፍነው።

ምስል
አዝነን አዝነን እኛም ገርጥተን   ሀዘን ሆነን አረፍነው። „አቤቱ ለምን ርቀህ ቆምክ?“ ምዕራፍ ቁጥር፲፩ ከሥርጉተ © ሥላሴ  Sergute © Selassie  21.02.2019 ከእመ ሲዊዘርላንድ። ግራጫማ መንፈስ ዘመነ ጃዋርውያን እንዲህ አና ብሎ ሲያውጅ አዝንን አዝነን እኛም የጠለሸ ግርጫማ ሀዘን ሆነን አረፍነው ደማችንም ማቅ ለባሽ። ይህ የሆነው ደግሞ ከሐምሌው ዝምታ በኋዋላ የሆነ ነው። ከዚያ በኋዋላ የሚሆነው ሁሉ ብልጭ ድርግም በሚል ናዳና ፈገግታ የዋጀው ነበር። በዛ የዕቀባ፤ የእግዳ ሰሞናት እንጨርሰዋለን ያሉት ነፍስን በፈጣሪ ጥበብ መትረፉ ሌላ ጥርስ አስነክሶ ሌላ ድቅድቅ ትዕይንት ቤተ መንግሥት አካባቢ ያው አፋኙ ቡድን ፈጠረ። አታስታውሱም ውዴቼ አንድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ጉባኤ ላይ አኮ የቀድሞዋ ደልዳለ እመቤት ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ ነበር ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት።  ስለምን ይህ ሊሆን ቻለ ብዬ ሁሉ ጽፌያለሁኝ በወቅቱ … ተወራራሽነት ያላቸው ሰፊ ምልክቶች ነበሩ። ከልቤ ሳዳምጠው በነበረው ጭብጥም ወስኜ የአብይ ዲታ መንፈስ ተጠለፈ ብዬ ጣፍኩኝ። መጣፍ ብቻ አይደለም ሁኔታውን በተደሞ አስቤበትም እንዲያው ለአንድ ዕውቅ የሰብዕዊ መብት ተሟጋች ደውዬ ተናገርኩኝ። በሳምንቱ እሱ እራሱ ኢትዮጵያ መግባቱን ሰማሁኝ። እኔ ኢትዮጵያ ለመግባት ስለመወሰኑ ምንም ዕውቅት አልነበረኝም፤ ግን መተንፈሻ ያጣው፤ ሚስጢር እንዳያወጣ ማዕቀብ የተጠለ በ ት ነፍስ እንዳለ ለሚያውቃቸው አካላት ሹክ እንዲል እና ሁኔታውን በወፍ በር እንዲከተተሉት ነበር ምኞቴ። ምክንያቱም „አክ“ ወሬ በሚል ስጋቱ ብን እንዲል ቅኖች ደግሞ ያን ጥርጣሬ ይታገሉት ስለነበር። የሆነው ግን ያ ዕውነት ነበር። ሁለት ነገር ነበር የተከሰተ

ዴሞክራሲ ሲቀርጡበት። ሳይቀጥሩበት ሳይቆርጡበት።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ዴሞክራሲ ሲ ቀ ርጡበት። ሳይ ቀ ጥሩበት ሳይ ቆ ርጡበት። „ፊታቸውን ሳይሆን ጀርባቸውን ሰጡኝ፤ በመከራቸውጊዜ ግን ተነስተህ አድነን ይላሉ።“   ትንቢተ ኤርምያስ ፪ ቁጥር ፳፯ ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie 20.02.2019 ከእም ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ዴሞክራሲ ነጭ ከረሚሎ ነው። ሁሉ ይወደዋል። ሁሉም ይሳሳለታል። ሁለም ሰፍ ብሎ  የትናጋው ማሟሻ  ያደረገዋል። እስታሁን ባለው ዘመን ስልጣንን ፈቅዶ በማስረከብ ኮ/ጎሹ ወልዴን አይተናል። የራስን ክብር ዝቅ አድርጎ ሌላውን ከፍ በማድረግ በዶር ለማ መገርሳ አይተናል።  እንዲሁም ሲነሪቲውም የመሆን መቻል አቅሙም እያለ እሱን እለፈኝ ብሎ ለኢትዮጵያ ሲባል እራስን ገርቶ በመገኘት ደግሞ በአቶ ደመቀ መኮነን አይተናል፤ የህውሃት የቆይልን ተማህጽኖ እያለም ግን በቃኝ ብሎ ሥልጣንን በፍሰሃ በማሰረከብም በአቶ ሃይለማርያም ደስአለኝም አይተናል። እንደ ድርጅትም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታሪኩን አሳልፎ በመሸለም እረገድ ብዴን አንደኛ ነው ዲከርድም በጣሽ ነው። ባይሆን ...  ሌላው የተወካዮች ምክር ቤት አብዛኛው እጅ የ108 ድምጽ ተቀብሎ ጠ/ሚሩ በሚሰጡት መመሪያ ሥር ራሱን አስገዝቶም አይተናል ከኮንፌድሬሽኗ ትግራይ በስተቀር። ዴሞክራሲ መራራ መሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ ህውሃት በአካል ያዬታዬበት ዘመን ይህ ነው። ፈተናውን ድርጅቱ ማለፍ አልቻልም።  ወደቀ ። ስለምን በፊትም አልነበረበትምና። 33ቱ አባላቱ የተቃወሙትን፤ በአብዛኛው ድምጽ የጸደቀውን የተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ አሻም ብሎ በድጋሚ ውይይት በማድረግ የበላይ አካሉን ውሳኔ አልቀበልም ሲል ዴሞክራሲ ቀድሞ ባልተፈጠረበት እና ባልነበረበት ሲዘመርለት