ልጥፎች

ከዲሴምበር 30, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የአቤቶ ኦፌኮን የሃሳብ አድራሻው የት ነው?

ምስል
የአቤቶ ኦፌኮን የሃሳብ አድራሻው የት ነው? „የሠራዊት ጌታ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል … ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ“  ሐጌ ፩ ከቁጥር ፭ እስከ ፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 30.12.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        ጠ ብታ። ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ? እንዴት ናችሁ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። ብቻ የትግራይ እና የኦሮሞ እናቶች የመንፈስ ብክነት፤ ጫን - ተደል ስጋት አሳስቦኝ ነው የሰነባበተው። ይላፍላችሁ ያላላቸው መከረኞች መቼም ናቸውና። ዛሬ በገረመኙ  የአምክንዮ ጥምዶች እና በፈጠጡ ሃቆች ዙሪያ አ ዳ ብዬ ሳይሆን አካል ተ- አማሳል አድርጌ ለማቅረብ አሰኘኜ እንዲህ … ·        ግ ን የኦፌኮን የሃሳብ አድራሻው የት ነው? ውዶቼ መቼም አዲስ አበባ እንደማትሉኝ ነው? ስለምን አቤቶ ኦፌኮን የሁለተኛ ጊዜ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ጥሶ ወለጋ መሄድን ደፈ ረው? ሰለለምን ተልዕኮ ነበር ነቀምት የሄደው? ለአቶ ዳውድ ኦነግ የመንፈስ  ጥሪት ምንጣፍ ለማንጠፍ? እኮ ስለምን?! ስለምን አርሲ አልሄደም? ስለምን ባሌ አልሄደም? ስለምን መቱ አልሄደም? ስለምን የጅጅጋ መከራ የደበደባቸውን ንጹሃንን አሳር ለመጋራት ወደ ዛ አ ላቀና ም? ስለምን ከሌሎች የኦሮሞ ድርጅቶች ተለይቶ የአቶ ዳውድ ኢብሳን ሞገደኛውን ኦነግን ጋር ለመሥራት ምርጫው ሆነ? ማንን ለማጥቃት? ማንን ለማንበርከክ? የማንን ቅ ስ ም ለመስበር? የማንን የፍቅር አቅርቦት ለመሰነጣጠቅ? ማንን ለማፈረስ? ዛሬ ጉዳዬ ይህ ነው - ሌሎችንም ጎበጥ ያሉ ሃሳቦች ይኬድባቸዋል … ሊንካቸውን ግን አለጥፍም። ምክንያቱም ይህን የመጠነ ሰፊ የሐሤት ሩህሩህ ዘመን ውስጥ ለማድረግ ለቆረጠ ሁሉንም መፈታ