ልጥፎች

ከጁን 3, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

እንዴት ሰነበታችሁ? "ፍቅር ሲያገረሽ፣ የዐብይ ሽማግሌዎች፣ ሶማሊያ ማን መክሯት ይሆን?" #Abiy, #Ethiopi...

ምስል

ለስህተት፤ ለግድፈት ትራስም፤ ፍራሽም ሌግዠሪ አንደበት አያስፈልገውም።

 ለስህተት፤ ለግድፈት ትራስም፤ ፍራሽም ሌግዠሪ አንደበት አያስፈልገውም። ንፁህ ፖለቲከኛ የፕሮፖጋንዲስትነት ተግባርም፤፦ምግባርም መናፈቁ ለዕንባ መድህኑ ሊሆን ፈጽሞ አይችልም። ስህተትን ያለ አቅም እና ወርዱ ማንጠራራት ተስፋን ጨምሮ #መናድን ያመጣል። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉ2024/06/02

#የኢትዮጵያ_86ቱ

ምስል
    ከአቶ መላኩ ደጀኔ ዬተገኜ ነው። ይህቺ ኢትዮጵያ ትናፍቃኛለች። ለጠቅላላ እውቀት #የኢትዮጵያ_86ቱ ብሄር ብሄረሰቦች መጠሪያ ስም:- 1. አማራ 2. ኦሮሞ 3. ትግራዋይ 4. ሶማሌ 5. አፋር 6. ሲዳማ 7. አገው 8. ዎላይታ 9. ከምባታ 10. ሀዲያ 11. ጋሞ 12. ጉራጌ 13. ኢሮብ 14. አርጎባ 15. ቱለማ 16. ስልጤ 17. ሺናሻ 18. አኝዋክ 19. ኑዌር 20. ሀመር 21. ኩናማ 22. ጉምዝ 23. በርታ 24. በና 25. አሪ 26. ሙርሲ 27. ቡሜ 28. ካሮ 29. ፀማይ 30. ኮንሶ 31. ዳሰነች 32. ቦረና 33. ጋብራ 34. አላባ 35. አርቦሬ 36. ባጫ 37. ቤንች 38. ባስኬቶ 39. ቡርጂ 40. ጫራ 41. ጋዋዳ 42. ጌዲኦ 43. ጊዶሌ 44. ጎፋ 45. አደሬ 46. ከፊቾ 47. ኮንታ 48. ኒያንጋቶም 49. ናኦ 50. ቀቤና 51. ሱርማ 52. ጠንባሮ 53. የም 54. ወርጂ 55. ዲዚ 56. ዶንጋ 57. ዳውሮ 58. ዲሜ 59. ምዓን 60. ኮሞ 61. ማረቆ 62. ሞስዬ 63. ኦይዳ 64. ቦዲ 65. ፈዳሼ 66. ኮሬ 67. ማሌ 68. ማኦ 69. መሰንጎ 70. መዠንገር 71. ቀዋማ 72. ቀጨም 73. ሸኮ 75. ዘየሴ 76. ዘልማም 77. ሽታ 78. ቤተ እስራኤል 79. ማሾላ 80. ኮጉ 81. ድራሼ 82. ገባቶ 83. ጌዲቾ 84. ብራይሌ 85. ሙርሌ 86. ኮንቶማ .... ናቸው። ************************ ምንጭ - የኢትዮጵያ ታሪክ፣ Sergute Selassie   · Shared with Public

#ቀይ ሽብር በኢትዮጵያ ተጀምሯል።

ምስል
  #ቀይ ሽብር በኢትዮጵያ ተጀምሯል። ሰማዕቱ ንገረው አዲስ (አቤል)በቀዬው በጥይት ተደብድቦ ተገድሏል። "ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ" (መጽሐፈ መክብብ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፪) #ጠብታ ። ሰማዕቱ አቶ አወቀም በመኖሪያ ቀበሌው በጨካኙ የሄሮድስ አብይ አህመድ አሊ ነፍሰ በላወች ተረሽነዋል። ይህን የእኛ አቤል ሰማዕቱ ንገረው አዲስ በአይኑ ተመለከተ። #የመከራ ደወል! ሰማዕቱ ንገሩው አዲስ የ13 ዓመት ታዳጊ ወጣት ነው። ታዳጊው ወጣት የ4ኛ ክፍል ተማሪ ነው። ሰማዕቱ፣ ተማሪው እና የበግ እረኛው ንገረው አዲስ እንደ ልጅ ተጫውቶ የማያውቅ፣ በቁም ነገር ላይ የሚያተኩር፣ ለጎረቤቶቹ በሙሉ ታዛዥ፣ ፍፁም ታታሪ እና ትጉህ እንደ ነበር ቤተሰቦቹ ለስላሳዋ ጋዜጠኛ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ አዳምጫለሁኝ። #አሰቃቂው ሂደት። ንገረው የእኛ አቤል በጎቹን በመጠበቅ ላይ ነበር። ጨካኞቹ የመንግሥት ኦነጋዊ ታጣቂወች ወደ ቀዬው ዘልቀው አቶ አወቀ የተባሉትን ነዋሪ "ፋኖ ነህ" ብለው ነፃ እርምጃ ይወስዱባቸዋል። #ቀይ ሽብር ማለት ነው። ንገረው ይህን ያያል። ይገድሉኛል ብሎ ይሸሻል የሚወዳቸውን በጎቹን ትቶ ሸሸ። ቤቱ ይርቅበታል። እሱ ይሮጣል፣ ገዳዮቹ ይከተሉታል። ንገረው በአቅራቢያው ካለው ጎረቤት ቤት ገብቶ *ቆጥ ላይ ይሸሸጋል። የልብኑ ምት እሰበው። ይህ አስጨናቂ ጊዜ ለብላቴናው ምን ያህል መርግ እንደሆነ እሰቡት። በተለይ ልጆች ያላችሁ። ብቻውን ነው። ወላጆቹን አልባ ጦርነት የተከፈተበት። ልክ ቤተ እስራኤሎች ይሳደዱ እንደነበረው ነው የሆነው። በህይወት አለመኖሩ እንጂ ቢተርፍልን ኖሮ የአና ፍራንክ ታሪክ በባዕታችን ይደገም ነበር። የቤተ - እስራኤል ልጆች እንደሚሳደዱት ነው የአማራ ልጆች እዬተሳደዱ ያሉት። ጭንቅላት ሳይሆን ህሊና

Die Regierung von Herods Abiy Ahmed Ali erschoss einen 13-jährigen Amhara-Schüler in der 4. Klasse.

  Sergute Selassie   · • Die Regierung von Herods Abiy Ahmed Ali erschoss einen 13-jährigen Amhara-Schüler in der 4. Klasse. Der Name des Jungen ist Negrewe Adiss. Er ist auch ein Hirte. Negerewe Adisse hütete die Schafe. Den Hirten Negerew mit eigenen Augen eine Trauer gesehen hat, als Herr Awke, ein Bewohner von #Qusquam Gemeinde getötet wurde. Die Attentäter waren die brutalen Soldaten von Herodes Abiy Ahmed. Also verliess Negrewe die Schafe und floh. Er floh, weil er den Mord gesehen hat. Negerewe Adisse verliess für immer die ihre Liebling Schafe. Negerewe Adisse hatte Angst vor den Soldaten. Er liess die Schafe zurück und floh. Die Soldaten folgten ihm. Negerewe Adisse ging auch zu einem Nachbarn in der Nähe. Negerewe Adisse versteckte sich dann. Aber die Attentäter holten ihn aus seinem Versteck, und sie schossen ihm in den Arm und die Stirn töte ihn. Die Mörder töteten ihn verantwortungslos und prahlten damit. Die Negerewe - Mörder bedrohten auch die Familien der Verstorbene

መጥኒ ለአንቺ ኢትዮጵያ።

  መጥኒ ለአንቺ ኢትዮጵያ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ክብሮች እንዴት አደራችሁ? ልዕልት ኢትይጵያስ እንዴት ነሽ? ስድብ፤ ክብርን መገሰስ፤ ማዋረድ ከዬት የመጣ መከራ ይሆን? ከሊቅ እስከ ደቂቅ የታረመ አንደበት #መነነ ። ይህ አሳረኛ ትውልድ ተፈርዶበታል። ስድብን እንዲያጠና፤ በስድብ ሪከርድ እንዲሰብር ይፈለጋል። ስድብን ትውልዱ አጥንቶ ባለ መዳያም እንዲሆን። ለዛም እንዲተጋ። መዘለፍ፤ መቀርደድ እንደ መልካም ነገር አናባቢም ተነባቢም አስተርጓሚም ተተርኋሚም አይደለም። ስድብ ማዋረድ እራስን ይሸረሽራል።    ከዚህም ባለፈ የቅኔ ያህል ስድብ ዘለፋ ክብር ተሰጥቶት አመሳጣሪም ያስፈለገው ይመስላል። እግዚኦ ነው። እራሱን በመሪነት ያስቀመጠ፤ ወይንም ያስቀመጠች ማንኛቸውም የስድብ የፊደል ገበታነትን መፍቀድ የተገባ አይመስለኝም። የትውልዱን የሞራል ግንባታ ያጫጫል። አማርኛ ቋንቋ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ለሆነው ማህበረሰብ ይሁን ላልሆነውም በስድብ፤ በዘለፋ የሚገኝ #ብቃትም #ላቂያነትም የለም። ኑሮም አያውቅም። ለትውልድ የሚሠራ ከሆነ የታረመ፦ ቁጥብ ያስተዋለ ሰብዕና ያስፈልጋል። በተለይ ወጣት ሆኖ ጊዜ ወደ መሪነት ካመጣው አላስፈላጊ ከሆኑ ከወጣትነት ሥነ - ምግባሩ ጋር መፋታት ይኖርበታል። ሊገራም ይገባል። "ቁመው የሰቀሉት ቁጭ ብሎ ……" እንዳይሆን።    ቢያንስ በመከራ ውስጥ በፈተና ውስጥ ላለ ማህበረሰብ ጥላ፤ ጋሻ የሚሆን መንፈስ መከራው እራሱ ትህትናን ስለሚያጎናጽፈው እራሱን ዝቅ አድርጎ አቅሙን ማፋፋት ይገባል። የሰው ልጅ ክቡር ነው። ፈጣሪ አላህ አክብሮ ቀድሶ መርቆ ነው የፈጠረው። ማንም ይሁን ማን፤ የትኛውም ክፍለ ዓለም የሚኖር የአለም ዜጋ በሰውነቱ #ሊከበር ይገባል። በውነቱ ገበሬም መሆን ሊቃለል አይገባም። "በማን

ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም

 ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም። ዕውነት ወለምታ ስለማይነካው። ዕውነት ጋራጅም አያሻውም። የሚወላልቅ፤ ተወላልቆ የሚገጥም #ብሎናም ስላልሆነ። ሥርጉ 2024/06/03

Elias and I have discussed a few of current Ethiopian issues ... ከኤልያስ አ...

ምስል