ልጥፎች

ከሜይ 10, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ለፖለቲካ እስረኞች ማን ይሆን ጠበቃው? ስለምንስ ከአጀንዳ ውጪ ሆኑ???? #አልገባኝም።

  ለፖለቲካ እስረኞች ማን ይሆን ጠበቃው? ስለምንስ ከአጀንዳ ውጪ ሆኑ???? #አልገባኝም ።   "የቤትህቅናት በላኝ።"   በሁሉም ዘርፍ ያለውን ሁነት ስከታተለው የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ #ባለቤት #አጥቶ ነው እምመለከተው። ሁሉንም አቅጣጫ ዳስሱት። በዬእስር ቤቱ ያሉ የፖለቲካ እስረኞች አጀንዳ የሚሆኑት በስሱ #የፍርድ #ቤት ቀጠሮ ሲኖራቸው ብቻ ነው። ይህ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ትግል #ያልተለመደ ተመክሮ ነው።    ምክንያቱም የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ በዬትኛውም የትግል መስመር ያሉ ተቋማት፤ ንቅናቄወች፤ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ #በኽረ #አጀንዳ ሆኖ ነበር እማውቀው። ከእስር ይለቀቁ ዘንድ ህብረ ድምጹ #አህቲ ነበር። አሁን ግን ያ ህብረ ድምጽ የለም። ለምን ይሆን? ጥናት ስላላደረኩበት ያ ነው፤ ይሄ ነው ልል አልችልም። የሆነ ሆኖ ቢያንስ #የእስረኛ ቤተሰቦች እንግልት ላይ ስለመሆናቸው እንኳን ጉዳይ ሊሆን አለመቻሉ ይጨንቃል። ልጆች ያላቸው የፖለቲካ እስረኞችም አሉ። እነኝህ የእስረኛ ልጆች በትምህርት ገበታቸው ላይ ሊያሳድር የሚችለው የሥነ ልቦና ጫናም ከፍተኛ ነው።   በሌላ በኩል ሁሉም እናት አለው እና ይህቺ #እናት በልጇ ሃዘን እንደ ተጎሳቆለች የሰይጣን ጆሮ ይደፈን እና አንድ ነገር ብትሆን #እርግማን ይሆናል። ጭራሽ በአብይ ዘመን የእስረኛ ፍቺ ድፍንፍን ያለ ጉድ ነው የሆነው። ምንም ፍንጪ የለም። ቢያንስ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋ ይሆን ዘንድ የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ በግልም ሆነ በጋራ በሰባዊነቱ አጀንዳ ሊሆን ይገባል ባይ ነኝ። እርግጥ ነው #የቅን እና #ቀና ዜጎች #ስጋት በስሱም ቢሆን ትንሽ ይገባኛል። ልፋታቸው ሆነ ድካማቸው አድማጭ ማጣቱ፤ ከእስር የሚፈቱ ወገኖች ለህዝብ ድካም ዕውቅና ለ...

ጥንቃቄ በማስተዋል ቢሆን ……

  ጥንቃቄ በማስተዋል ቢሆን ……   ሃኪም ቀስብለው ተራምደው አያውቁም ችግርን ለመፍታት፤ ለህይወት ለመድረስ መጣደፍ ነው። ይህ ጸጋ ግሎባልም ነው። ጥሪያቸውም ነው። #ብሩኮች ።    "ቤት በጥበብ ይሠራል፤ በማስተዋል ይጸናል።" (ምሳሌ ምዕራፍ 24 ቁጥር ፫)   የኢትዮጵያ ሃኪሞች እጅግ ሐዋርያ ከሆነ ትዕግሥት በኋላ፤ ዕውነት የሆነ ጥያቄያቸውን ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ለአብይዝም መንግሥት አቅርበዋል። ጥያቄው ትክክለኛ እና ዕውነትን የገለጠ አቤቱታ ነው። ነገር ግን ጥያቄው አቅጣጫውን ስቶ ካለስኬት ተዳፍኖ ጉዳት አምራች እንዳይሆን ብርቱ ጥንቃቄን ይሻል።   "ጠቢብ ሰው ብርቱ ነው፤ ዓዋቂም ሰው ኃይሉን ያበዛል።"    ከሃኪምነት በላይ ምድራዊ ልቅና ያለው የለም የሚል እምነት አለኝ። ከእግዚአብሄር በታች ሩኃችን በህክምና ባለሙያወች መዳፍ ላይ ነውና። ለእነሱ በምንም ሁኔታ ፕሮፖጋንዲስት አያስፈልጋቸው። ለገኃዱ ዓለም የሩህ መሪ ናቸውና። አዛኞች፤ አጽናኞችም። አይደለም ስለራሳቸው ስለእኛም የቅዱስ ሩፋኤል ሥልጣን የተሰጣቸው ናቸው እና። ፀጋቸው ሰማያዊ። ጥሪያቸው ሰባዕዊ ነውና። በአቤቱታቸው ላይም የጋመ ነዲድ፤ ወይንም እንክርዳዳ መቀዬጥ የተገባ አይመስለኝም። ታቅዶም ይሁን ሳይታቀድ። አቤቱታቸው #ንጽህናውን የጠበቀ ድንግል ነውና ምንም ቅጥያ ፍላጎት ሊቀጣጠልበት አይገባም።    #ሦስት ጉዳዮችን ለማጣቀሻ አቀርባለሁኝ።   1) ታስታውሱ ከሆነ በአንድ ወቅት አዲስ አበባ ከተማ ላይ "ለመስቀሉ እሮጣለሁ" የሚል መንፈሳዊ መልዕክትን በቅድስና የያዘ መሰናዶ ተጀመረ። እራሳቸው ሠርተው አቅም #መፍጠር የተሳናቸው ፖለቲከኞች፤ ቲ ሸርቱን አሰርተው መሪው እኛ ነን የማለት ያህል ማህበራዊ ...

የማያረጀው የህወሃት #አሳቻ አና #አዘናጊ ቧልት። ህወሃት በመግለጫ የወጣለት #አክሮባቲስት ነው።

  የማያረጀው የህወሃት #አሳቻ አና #አዘናጊ ቧልት። ህወሃት በመግለጫ የወጣለት #አክሮባቲስት ነው።    ዝም ብላችሁ ስታስቡት ሙሉ ፶ ዓመታት ኢትዮጵያ ምን ያህል ትሬኮላታ ሃሳብ ያዘለ መከራ ተሸክማ እንደ ኖረች ማመሳጠር ትችላላችሁ። ከዕዳም #የበለዘ እና #የማረተ ዕዳ።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   ህወሃት ከፍጥረቱ እስከ ልደቱ፤ ከልደቱ እስከ ወጣትነቱ፤ ከወጣትነቱ እስከ ጉልምስናው፤ ከጉልምስናው እስከ እርጅናው፤ ከእርጅናው ምንአልባትም እስከ ህልፈቱ አሳቻው የህወሃት ቧልት ይቀጥላል። የሚገርመኝ ሴራ የዘለቀውን የነፍስ አድን ጥሪውን ተቀብለው መንፈሳቸውን የሚገብሩ ሰብዕናወች መኖራቸው ነው።   ህወሃት እንደ #እስስት ቀለሙን እዬቀያዬረ የፍዳ ማምረቻ ተቋምነቱ ቀጣይ ነው። መጥኒ አንቺ ኢትዮጵያ - የፈረደብሽ። በቅርቡ የመስተዳድር መሪ ለውጥ በውል ተደመጠ። አሁን እቴጌ ትግራይ በአዲስ አመራር ላይ ናት። ያው ዕድሏን ትሞካክረው እስኪ ፈጣሪ ይርዳት ብዬ ዝም ነው ያልኩት።    ይህም ሆኖ በእቴጌ ትግራይ በዕድሏ፤ በዕጣ ፈንታዋ ላይ ግን መሪወቿ #አሳቻ ቧልታቸው ቀጥለዋል። ያለ መግለጫ አልባ ለህወሃት ህልፈቱ ነው። እንደምን መሽቶ ይነጋለታል? #ሱሱ መግለጫ ነው። የሚገርመው ጸንቶ የሚቆይ መንፈስ በመግለጫው አለመኖሩ ነው። የህወሃት መግለጫ የወጣለት አክሮባቲስት ነው። የህወሃት አካል ጥዋት አንድ ከሰዓት ከብት ግባት ማታ ለእንቅልፍ መዳህኒት ሌላ መግለጫ የተለመደ ነው በተለያዬ ሥያሜ።   የወረቀቱም የቀለሙም መከራው ጠንቷል። ህወሃት ዘለግ ያለ ምኞት ነው ያለው። አይደለም ዛሬ ሥልጣን ላይ እያለም ኢትዮጵያን እዬመራም፤ እስከ ጋንቤላ መጠነሰፊ ምኞት ነበረው። የወተት ...