ልጥፎች

ከጁን, 2021 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሰባዕዊነት ስዋሰዊነት ነው። የጸጋዬ ራዲዮ የ24 06 2021 የራዲዮ ፕሮግራም።

ምስል

የዶር አርከበ ዕቁባይ ሦስት ዓመት ልባም ጥሞና ለስኬት።

ምስል
  እንኳን ወደ ከበቡሽ ሚዲያ በሰላም መጡልኝ።   ·        የ ዶር አርከበ ዕቁባይ ሦስት ዓመት ልባም ጥሞና ለስኬት።   ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠበቂ በከበቡሽ የቁራሽ አንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ።   „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል። “   ·        ማ ዕዶተ ጠባቂ ማናቸው አጀንዳወች ይለፍ የሚሰጥ ዕልፍኝ። ዶር አርከበ እቁባይ የተመደ UNIDO ከመጨራሻወቹ ሦስቱ እጩወች አንዱ መሆናቸው ተደምጧል። የተባበሩት መንግሥታት የኢንደስትሪ ተቋም UNIDO በዳይሪክተርነት ለመመራት ነው የታጩት። ዕንቁ ዕድል ነው። ለጭምት ፖለቲከኛ ይህ ከዕድልም በላይ ነው የሰማይ ስጦታ። አክብረው፤ ጥሞና ወስደው ሊቀበሉት ይገባል። ጸጸትንም ሊመግቡት ይገባል። ለፈጣሪ ከሳው ያ ነውና። እያንደንዱ ልጅ ሲወለድ መክሊትም መልዕክትም ይዞ ይወለዳል የምለውም ለዚህ ነው። የአፍሪካ ህብረት አህጉሩን ወክለው እንዲወዳደሩ በእጩነት እንዲቀርቡም ወስኗላቸዋል። ከጀርመን እና ከቦልቡያ ጋር እኩል ተወዳዳሪ ናቸው ዶር አርከበይ እቁባይ ኢትዮጵያን ወክለው። ·        የ እጬጌው ሂደት የቤት ሥራ። ነገስ ዛሬ ፈቅዳ እና ወዳ በሥሞ ኢትዮጵያ ለምትሳጣቸው ይህ ሰማይ ጠቀስ ክብር ውለታዋን ይመልሱ ወይንስ ውለታ ቢስ ይሆኑ ይሆን? እጬጌው ሂደት ይመልሰው። ልዕልት ኢትዮጵያስ አመድ አፋሽ ወይንስ ሞገስ አፋሽ ያደርጓት ይሆን? በጭንቋ፤ በመከራዋ፤ በመከፈቷ፤ በልጆቿ ዕንባ ለሁሉም እኩል ደራሽ፤ ተቆርቋሪ ይሆኑ ወይንስ ይክዷት ይሆን? የእናት ኢትዮጵያ ጥቃት አውጪ ወይንስ ተበቃይ ይሆኑ ይሆን? ጭምትነታቸው፤ ስክነታቸው ለራሳቸው ሰብዕና? ለድርጅታቸው

“የዘር ማጥፋት የለም” ፕ/ር ካዱ ወይስ ፈሩ #Prof_Berhanu_Nega

ምስል

Reyot የኢዜማ የዘር ማጥፋት ክህደት ስረምክንያቶች… አደባባይ የተሰጣው የብርሀኑ ነጋ ሰሜን ጠልነት 06/15/2021

ምስል

በእልኸኝነት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አገር አጥተን እንደ ኩርድሾቹ … ? እናት ዓለም ገናናው ሥምሽ በክብርሽ፤ በሞገስሽ ልክ ይቀጥል ይሆን?

ምስል
    እንኳን ወደ ከበበቡሽ ብሎግ በሰላም መጡልኝ።   በእ ልኸኝነት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አገር አጥተን እንደ ኩርድሾቹ … ? ·       እናት ዓለም ገናናው ሥምሽ በክብርሽ፤ በሞገስሽ ልክ ይቀጥል ይሆን? ዕለተ አርብ ማዕዶተ - ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚመራራ። „ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።“ (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ 3 ቁጥር 17)   ·       ጠ ብታ! እንዴት አደራችሁ ቅን ቤተሰቦቼ? ልዕልት ኢትዮጵያስ እንዴት አለሽልኝ ናፍቆት ዓለሜ? ·       እ ፍታ ለአንድ አፍታ።   እልኸኝነት አቅም ሲኖርህ ቢያምርም ቢከፋም ሞክረው። አቅም በሌለህ ሁኔታ በባዶ እጅ እልኽኝነት ሽንፈትን ቢደርብ እንጂ አትራፊ አይሆንም። ለነገሩ እልህ አይደለም ለብሄራዊ ጉዳይ ለሦስት ጉልቻም አይሆንም። እልህ ከሦስት ጉልቻ ዝቅ ላለው የግል ማህበራዊ ግንኙነትም አይረዳም። ወጣት ሳይሆኑ የወጣት ባህሪን፤ ጎረምሳ ሳይሆኑ የጎረምሳን ባህሬ፤ ኮረዳ ሳይሆኑ የኮረዳን ባህሪ ሁነኝ ማለት የዕድሜ ጸጋ እና በረከትን ካለማገናዘብ የሚመነጭ ይመስለኛል። ይመስለኛል እኔ በጹሑፎቼ አዘውትራለሁኝ። ይሕ የሆነበት ምክንያት ጥናታዊ ተግባር ያልፈጸምኩበት ስለመሆኑ ለማጠዬቅ ነው። የሆነ ሆኖ የ60/የ70/የ80 ዓመቱ ፖለቲከኛም እልኸኛ ነው። ጎረምሳም ኮረዳም ልሁን ባይ ነው። ከልጆቹ፤ ከልጅ ልጆቹ እኩል። የሚገርመው እልኸኝነቱ ያበቀለ ቢኖረው መልካም በሆነ ነበር። የተካው እሳት የላሰ ወጣት ቢኖርም ይሁን እንበለው። ግን የለም። አንዳቸውም የላቸውም።   ምክንያቱም ተተኪ ማፍራት ፕሮጀክታቸው አይደለም። የሚፈሩትም ይኽነኑ ነው። ፕ/መራራ ጉዲና፤ ፕ/ በዬነ ጴ