ልጥፎች

ከጁን 17, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

መጥኒ ለእናታዊነት።

ምስል
  መጥኒ ለእናታዊነት።   • ዘገባው የBBC ነው።   "በትግራይ ከሥራ ቦታ፣ ከመንገድ እና ከመኖሪያ ቤት እየተካሄደው ያለው አፈሳ የፈጠረው ስጋት"   https://www.bbc.com/amharic/articles/c3vywvgnv2qo «የትግራይ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በትግራይ "የተመለመሉ" ወጣቶችን ለሠራዊት እያሰለጠነ መሆኑን ለቢቢሲ ትግርኛ ገልጾ የምልመላው ሂደት ግን "በክልሉ መንግሥት እንደሚፈፀም" ተናግሯል።   ቢቢሲ ያነጋገራቸው በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ወጣቶች ከሥራ ቦታቸው፣ ከመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም ከሕዝብ ትራንስፖርት ላይ በግዳጅ ተወስደው ወደ ተለያዩ ካምፖች መላካቸውን ተናግረዋል።   ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ በበኩሉ የትግራይ ፀጥታ ኃይሎች በክልሉ መጠነ ሠፊ አፈሳ እና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እያካሄደ መሆናቸውን በመጥቀስ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።   የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጊቶቹ ይፈጸምባቸዋል በሚል ከዘረዘራቸው አካባቢዎች መካከል፣ ሰሜን ምሥራቅ ዞን፣ ማዕከላዊ ዞን እና ምሥራቃዊ ዞን ይገኙበታል።   ለሁለት ዓመታት የተካሄደውን ጦርነት ባስቆመው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ሥልጣን ከያዘ በኋላ በህወሓት መሪዎች እና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ውጥረት ተፈጥሯል።   ተመልሶ ሥራ የጀመረው ፈርሶ የነበረው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ሕጋዊ የፓርቲ ዕውቅናው የተሰረዘበትን የህወሓት ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ የሾመ ሲሆን፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ያሉበት ሁኔታ አስካሁን በይፋ አይታወቅም።   በዚህም የተነሳ በክልሉ ሌላ ...

፲ #ኤርትራ፤ ፳ ሰሜን ሱዳን፤ ፴ ግብጽ አያስደነግጡኝም - እኔኑ። #ለምን? #ይልቁንስ እኮ ……… #ምን???

ምስል
  ፲ #ኤርትራ ፤ ፳ ሰሜን ሱዳን፤ ፴ ግብጽ አያስደነግጡኝም - እኔኑ። #ለምን ? #ይልቁንስ እኮ ……… #ምን ???   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"     #ምዕራፍ ፲፱።   ፲ #ኤርትራ ፤ ፳ ሰሜን ሱዳን፤ ፴ ግብጽ አያስደነግጡኝም - እኔኑ። ለምን?    ፈላስፊት ኢትዮጵያ ------አትለካም። ሳይንቲስቷ ኢትዮጵያ -------አትሰፈርም። ዩንቨርሷ ኢትዮጵያ --------አትመዘንም። ህጊት ኢትዮጵያ ---------አትገመትም። ቤተ - ይሉንታዊቷ ኢትዮጵያ ------------- #አትከነዳም ።   ሱዳንም በቀደመው ጊዜ ወራ በመተማ በኩል፤ ግብጽ ዕድሜ ልኳን ታግላ፤ በዞግ አደራጅታ ባህር በር ይሁን ወደብ አሳጥታ፤ የአፍሪካ ቁልፍ ቀንድነቷን ፈትና፤ ኢትዮጵያ ግን አለች የአፍሪካው ህብረት #ዋና ጽህፈት ቤት ሆና፤ የዓለም ፬ኛ #የዲፕሎማሲ ዓይንም ሆና ቀጥላለች።   ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያኒዝም እንደ አሻው በሆነ አካል የሚኮሰምን፤ #ቃ የሚል፤ #ዳ የሚፈትነው፤ ስብራት የሚጎበኜው ማንነት አይደለም። ብዙ ያለው፤ ያለውን ልቅና በልዕልና መስጥሮ የተቀመጠ አንቱ ማንነት ነው ኢትዮጵያዊነት። የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና " #በደራሽ ሱናሜ፤ በምኞት ፈረስ ፍርስርሱ ይሁን ብትንትኑ የሚወጣ" ማንነት አይደለም ተፈሪው ኢትዮጵያዊነት።   በብልጽግና ዘመን እራሱ እኮ ብዙ ፈተናን አስተናግዷል። ተቋማቱ ሁሉ ፈተና ላይ ነው የባጁት። የኢትዮጵያኒዝም አማንያን ያላዩት የአሳር፤ የፍዳ ዓይነት የለም። ሎጎወች ኢትዮጵያን ከሚገልጹ ንጥረ ነገሮች ሁሉ በእጅጉ ከድንቁ የኢትዮጵያዊነት ማንነት የራቁ ናቸው። አንድ ቀን ለራሳቸው ለጠቅላይ አብይ አህመድ ሰባስቤ አቀርብላቸዋለሁኝ። በዚህው በቤተ ሥርጉትሻ።...

#ሁለት ወዶ አይሆንም።

  #ሁለት ወዶ አይሆንም።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።"   ምዕራፍ ፲፰።   #ብልፄው ሁለት ወዶ አይሆንም። ሥልጣኔ #ይጽና በደልም #ይቀጥል አያዋጣም።   የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች #ካቴና ሊነካቸው አይገባም። ምክንያት ከፖለቲካ #ውክልና ፤ ከመኖር አንባ ውስጥ #ተገለዋል ።   ምን #አደረጉ ? መገደላቸውን፤ ለቅሷቸውን፤ መገፋታቸውን፤ መቃለላቸውን ሁሉ ቻል አድርገው በተቀመጡ ለምን #ካቴና ይታዘዝባቸዋል?   አንድ ጊዜ አይደለም፤ ሁለት ጊዜ አይደለም በተደጋጋሚ ብልፄው ተኝቶ ሊያስበው የሚገባው ቁምነገር በቅድስት ኦርቶዶክስ ላይ በግልጽም በስውርም የከፈተው ዘመቻ ሊቆም ይገባል።   ቅድስቷ ይቅርታ ልትጠየቅ ይገባል። በይፋ። ላዘኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ብቻ ሳይሆን፤ ለወዳጆቿም ጭምር አጽናኝ ብሄራዊ መልዕክት በእጅጉ ያስፈልጋል። #ይቅርታ መጠየቅ #እርቅን ፤ መተማመንን ቢያጸድቅ እንጂ ማንንም አይጎዳም። የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የጸጥታ ህማማት ሊያመጣ የሚችለው እርግማን ሊታሰብ ይገባል።   ለትውልድም ለአገርም #ስለማይጠቅም ። ውዶች ክብሮች ቤተ ሥርጉትሻ እንዴት አላችሁልኝ። .   ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።   ኑሩልኝ። አሜን። ሥርጉተ©ሥላሴ። Sergute©Selassie. 15/06/026.   #ፍቅር ሲያልቅ #ትዕግሥት #ይሰደዳል ።