#ሁለት ወዶ አይሆንም።

 

#ሁለት ወዶ አይሆንም። 
 
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።"
 
ምዕራፍ ፲፰።
 
#ብልፄው ሁለት ወዶ አይሆንም።
ሥልጣኔ #ይጽና በደልም #ይቀጥል አያዋጣም።
 
የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች #ካቴና ሊነካቸው አይገባም።
ምክንያት ከፖለቲካ #ውክልና፤ ከመኖር አንባ ውስጥ #ተገለዋል
 
ምን #አደረጉ? መገደላቸውን፤ ለቅሷቸውን፤ መገፋታቸውን፤ መቃለላቸውን ሁሉ
ቻል አድርገው በተቀመጡ ለምን #ካቴና ይታዘዝባቸዋል?
 
አንድ ጊዜ አይደለም፤ ሁለት ጊዜ አይደለም በተደጋጋሚ ብልፄው ተኝቶ ሊያስበው
የሚገባው ቁምነገር በቅድስት ኦርቶዶክስ ላይ በግልጽም በስውርም የከፈተው
ዘመቻ ሊቆም ይገባል።
 
ቅድስቷ ይቅርታ ልትጠየቅ ይገባል። በይፋ። ላዘኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
አማኞች ብቻ ሳይሆን፤ ለወዳጆቿም ጭምር አጽናኝ ብሄራዊ መልዕክት በእጅጉ ያስፈልጋል።
#ይቅርታ መጠየቅ #እርቅን፤ መተማመንን ቢያጸድቅ እንጂ ማንንም አይጎዳም። የቅድስት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የጸጥታ ህማማት ሊያመጣ የሚችለው እርግማን ሊታሰብ ይገባል።
 
ለትውልድም ለአገርም #ስለማይጠቅም
ውዶች ክብሮች ቤተ ሥርጉትሻ እንዴት አላችሁልኝ። .
 
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
 
ኑሩልኝ። አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ።
Sergute©Selassie.
15/06/026.
 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።