ልጥፎች

ከጁላይ 6, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሃሳብ ጎዳና መሪ ነው፤ ስለምን ይፈራል?

  ሃሳብ ጎዳና መሪ ነው፤ ስለምን ይፈራል?   "በመጀመሪያ #ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሄር ዘንድ ነበር፥ #ቃልም እግዚአብሄር ነበር። ይህ   በመጀመሪያው በእግዚአብሄር ዘንድ ነበር። "   (ቅዱስ ዮሐንስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፩ - ፫።)   #ምዕራፍ ፲፱።   ሃሳብ ስለምን የቂም ፈል ማምረቻ - ለምን ይሆናል? ሃሳብ የፖለቲካ #መበቃቀያ ---- ስለምን ይሆናል? ሃሳብ ስለምን እንዲታመቅ ወይንም እንዲታቆር ይፈለጋል? የልዩነት ሃሳብ #ጠሐይን እንዳያይ ለምን ይበየንበታል?   ሃሳብ ወልጋዳ እንኳን ቢሆን ገርቶ ህዝብ ጠቀም ለማድረግ እንዴት ያቅታል? ለመሆኑ ፖለቲካ ለሙጃው ወይንስ ለአቦካዶ? ፖለቲካ ለበቀል መፈልፈያ ወይንስ ለአብሮነት ማብቀያ? ፖለቲካ ለተፈጥሮ ህልውና ወይንስ ጥቃትን ለማበረታታት? ትትርናው ሃሳብን #በድቅድቅ ጨለማ እንዲከዘን ስለምን ይፈረድበታል?   #ሰው ምንድን ነው? የቃል ስክነት አይደለንም? ቃል እኮ ሃሳብ ነው። ግን ግን ……… ሰው የሃሳብ ውጤት አይደለምን? " ሁሉ በእርሱ ሆነ፤ ከሆነውም አንዳችስ ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። በእርሱ ህይወት ነበረች፥ ህይወትም የሰው ብርሃን ነበረች። ብርሃንም በጨለማ ይበራል። ጨለማም አላሸነፈውም። (ቅዱስ ዮሐንስ ከምዕራፍ ፩ ቁጥር ፫ - ፭) እኮ ጋብቻ ምንድን ነው?   ጋብቻ ከሃሳብ አይደለምን የሚነሳው? እናስ --- ጋብቻ የትውልድ መሠረት አይደለምን? ሥልጣኔ - ታሪክ - ሃይማኖት - ባህል - ወግ - ልማድ ትውፊት - ዕምነት - ዕውቀት - መኖር - የሃሳብ ውጤቶች አይደሉምን? ይህ ከሆነ ለምን ሰው የተሰጠውን የማሰብ አቅሙ #ይታሠርበታል ? የማይገባኝም እንዲገባኝም የማልፈቅድለት በሃሳብ ዙሪያ ታቅዶ ...

የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ #ዕውቅና የመስጠት። …

ምስል
  የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ #ዕውቅና የመስጠት። …   • … በዛ ልክ ፍላጎትን የማደራጀት አስፈላጊነት ቁርጥ ይህን #ጭብጥ #ይመስላል ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ብዙ ዓይነት #መሻቶች አሉ። መሻቶቹ ዕውን ሊሆኑ የሚችሉት የዘመኑ የፖለቲካ ባህሬ #በሚፈቅደው ልክ ከተደራጁ ብቻ ይሆናል። አንዳንድ የዘመኑ የፖለቲካ ባህሪያት #ዘለግ ያለ ጊዜ ሊቆዩ ይችላሉ።   አንዳንዶቹ ደግሙ #አጭር ጊዜ ሊወስድባቸው ይችላል። በዛ ልክ መሻት #ተደራጅቶ ከተመራ መሻት ከግብ ይደርሳል። በስተቀር መሻት #ተንሳፎ ይቀራል። #ፋንታዚ ሆኖ። ለዚህ ነው ደጋግሜ ስለዘመኑ ባህሬ ዕውቅና ስለመስጠት እና ማድመጥ እንደሚገባ አበክሬ የምገልጸው።   የፈለገ #ዕንቁ ሃሳብ፤ ህዝብ ጠቀም፤ ተፈጥሮ ጠቀም፤ ሐሤት አፍላቂ፤ ሰላም ዓዋጅ ይሁን፤ የዘመኑ ባህሪ ካልፈቀደ #ውትልፍ የለም። ከዘመኑ ባህሬ ያፈነገጡ መሻቶች ሳይሳኩ ሲቀሩ ደግሞ የሥነ - ልቦና ችግር ይፈጥራል። ተስፋ #ቆራጭነት ይሰፍናል።    ያለንበት የዘመኑ ባህሪ #ተለዋዋጭ ፤ #ቅጽበታዊ እና #ድንገተኝነት ይታይበታል። በባህሬው ልክ መፍጠን ካልተቻለ የተስፋ ሹልከት ይገጥማል። የዘመናችን ትንፋሹ የሚለካው በዘመኑ የፖለቲካ ባህሬ ፍሬም ወርክ ነው። ባለፈው የአረብ ኢምሬት የተከታታይ ውሳኔወችን ያን መነሻ በማድረግም አጠናክሬ መፃፌ ይታወሳል።    አንድ ጊዜ "ድርድር #ፖለቲካ ሆኖ" ደግሞ ተብሎ ስላቅ ቢጤ ነበር። ያሉትን የኢትዮጵያ ፖለቲከኛ ሳስብ ሁልጊዜ ይገርመኛል። አይደለም ለፖለቲካ ለትዳር፤ ለመኖር፤ ለዕውቀት፤ ለሽያጭ እና ለግዥ ድርድር አውራ ነው። ለዛውም በዚህ ቆሞ በማይጠብቅ ተለዋዋ...

#የማያስቆጭ ጊዜ ኖርዌ ብራዚልን አሰናበተ። የብራዚል ህልም መነነ።

  #የማያስቆጭ ጊዜ ኖርዌ ብራዚልን አሰናበተ። የብራዚል ህልም መነነ። በዛሬው ጨዋታ 82 ሺህ ህዝብ ነው የተገኜው። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። እንኳንም አመሸሁ። እንኳንም አየሁኝ። የማያስቆጭ ጊዜ። የብራዚል የእግር ኳስ ቲም ብስጭቱን መቆጣጠር አልቻለም። በመጨረሻ #የቅጣት ምት አግኝተው አንዷን ጎል ተቀይሮ ለገባው ለኒማር ተሰጠው። እንደ ማጽናኛ ባዶ እጁን እንዳይመለስ። ጨዋታ እንዲህ አቅልን አንጠልጥሎ፣ በድንገቴ እያንበሸበሼ ስኬቱን ሲያበስር ማለፊያ ነው። ድንቅ ጊዜ። ፍልሚያው የሚገርም ነበር። የኖርወይ ጎል ጠባቂው ኳሷን ከእሱ በማራቅ ሥራውን #ያቃለለበት ሂደት ዕፁብ ነበር። ኖርወይ #ሁለት ብራዚል #አንድ ። ኖሮይ በቁርጥ ቀን ልጇ ሁለት ጎል በተከታታይ። የኳሷ የሁለተኛዋ የመረብ #ስምረት ውብ ነበር። ግን ያስጨንቅ ነበር። የዓለም ዋንጫ ጨዋታን ሲቀላቀሉ ኖሮወዮች በሙሉ ዝግጅት፣ ባህላቸውንም ጭነው፣ አክብሮት ነበር ከአገራቸው የተነሱት። እንዳስደመሙን ቀጠሉ። #ዕድሉን አከበሩ። #ድሉንም ሰበሰቡ። ሥርጉትሻ 06/07/026. #ኳሲዝም ለምልሚ። See less