#ተናፍቃችኋል። አቶ ኦባንግ ሜቶ የሰባዊ መብት ዓራት ዓይናማ ሞጋች። ዶር ኮንቴ ሙሳ ጭምት ፖለቲከኛ። ጋዜጠኛ ተመስገን ደስአለኝ ትጉህ ሞጋች ሃያሲ ጸሐፊ። ፖለቲከኛ አቶ ክንፋ አሰፋ አምደኛም።
ለነፃነት ትግል ሊቀ - ትጉኃን የሆናችሁ ወንድሞቼ ሆይ! ድምፃችሁ #ናፈቀኝ የት ይሆን ያላችሁ? #ተናፍቃችኋል ። • የመደመር መንግሥትን በግልባጩ ላንብበውን? "ሥጋን እንጂ ነፍስን መግደል የማይችሉትን አትፍሯቸው።" (ማቴ ፲፡፳) #ምዕራፍ ፲፱። #እፍታ ። መፈላለግ፤ መጠያዬቅ፤ መተሳሰብ ትውፊታችን ነው። ትውፊታችን ማስቀጠል ደግሞ ግዴታችን ነው። ለረጅም ጊዜ አቶ ኦባን ሜቶን አስመልክቶ ፌስቡኩኑም፤ ኤክስ አካውንቱንም ፈታትሼ የት ነህ የሚል ጥያቄ ሳቀርብ ነበር። ድምጹ ከለት ወደ ዕለት እዬራቀ ሲሄድም እንደ አንዲት ኢትዮጵያዊት እህት ሲጨንቀኝ ጭንቀቴን ተጋሩ ብዬ በፔጄ ላይ ስጽፍ ቆይቻለሁኝ። አሁን ከምርጫ በኋላ በአንድም በሌላም ላያቸው እችል ይሆን ብዬ አስቤ ነበር። ግን አላየኋቸውም። ስለሆነም በጸረ ህወሃት ትግል ትጉህ የነበሩ ወገኖቼን በጥልቀት አሰብኳቸው። #ቆጥረን ባንሰጥም። 1) አቶ ኦባንግ ሜቶ የሰባዊ መብት ዓራት ዓይናማ ሞጋች። 2) ዶር ኮንቴ ሙሳ ጭምት ፖለቲከኛ። 3) ጋዜጠኛ ተመስገን ደስአለኝ ትጉህ ሞጋች ሃያሲ ጸሐፊ። 4) ፖለቲከኛ አቶ ክንፋ አሰፋ አምደኛም። አቤቱ አጤ "መደመር፤ የመደመር ትውልድ፤ የመደመር መንግሥት።" እነኝህን ሊቀ - ትጉኃን የአገር ልጆችን #ቀነሰ ወይንስ አከለ? አፋፋ ላይ አስቀመጠ ወይንስ አገተ? አጠነከረ ወይንስ #አቀበ ? አሰበለ ወይንስ አጠወለገ? የሚለውን አደባባይ ላይ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን ልንጠይቃቸው፤ ልንሞግታቸው ይገባል ባይ ነኝ። ጠቅላይ ሚኒስተሩም እንደ ቀደምት መሪወች "ላም እረኛ ምን አለ?" ብለው ጆሯቸውን ዘንበል አድርገው ሊያደምጡን፤ መልስም ሊሰጡን ይገ...