ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 3, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

መጥኔ ለአማራ እናት።

ምስል
 

ምጽዐተ ጎንደር።

ምስል
 

ብላሹ ክፋ ሃሳብ። Ein böser Gedanke hat keinen Nutzen. Schmerzbelastung.

ምስል

የኔታዋ የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት የምህላ ተደሞ ጎንደር በአርምሞ! ከጥቅምት 01 ቀን እስከ ህዳር 10... ይህ ፀጋ ነው አሁን አናርኪዝም የሚባል ባላንጣ እንደ #ዳንቴል በእጅ ተሠርቶ ከፈጣሪዋ ጋር ጎንደርን እዬነጠላት የሚገኜው።

ምስል
ይህ ፀጋ ነው አሁን አናርኪዝም የሚባል ባላንጣ እንደ #ዳንቴል በእጅ ተሠርቶ ከፈጣሪዋ ጋር ጎንደርን እዬነጠላት የሚገኜው። ጎንደር እንደ እኛ እንደ እያንዳንዳችን የሚቀናባት #በዕት ናት። ማይክ የያዘ ሁሉ ሲያብጠለጥላት ውሎ ያድራል። ከዛች በዕት የተገኙ ልጆቿም ቀና ባሉ ቁጥር ቅጥቀጣው፤ እገታው የላይኛው ያውቀዋል። እነሱም ችግሩ እራሱ አኃቲ ልቦና ፈጥሮላቸው አይተዛዘኑም።   ልጆቿም የሌላ #ጌጥ ናቸው እንጂ ስለ እትብቴ የተቀበረባት ብለው አስበው አያውቁም። የራሷ ልጆች እየገፏት እሷ ግን አክብሮት #ነፍጋቸው አታውቅም። የጎንደር #ሳቋ #የሚኮሰኩሳቸው በርካታ ናቸው። ሳያውቋት ሂደው ሳያዮዋት ግን ማቱን ሲያዝንቡባት ውለው ያድራሉ። አንድ ፔና ያልገዛ አንጋች ካልሆንክ ብሎ ልጆቿን ቁሚ ተቀመጪ ሲላት ውሎ ያድራል።ይህ ሁሉ ተከማችቶ እንሆ ጎንደር የሥርዓት አልበኞች መፈንጫ #ትንሿ #መቋድሾ ሁና አረፈችው። እንደ ተመኙት አደረጉት።   ይገርሙኛል የክፋ ሃሳብ ድውያን የማይገናኜውን አምጥተው አገናኝተው ጎንደርን ሲዘለዝሉ፤ ሲያዘላዝሉ እንደምን ችለው ቤተሰቦቻቸውን እንደሚመሩ ሁሉ ይገርመኛል። ጎንደር ወደምድር ብትሰምጥ ወይ ብትተን ይመኛሉ። ለዚህ ብቻ የተፈጠሩ እስኪመስለኝ ድረስ። ዝም እምለው ክፋ ሃሳብ ትርፋ ክፋት መሆኑን ጠንቅቄ ስለማውቅ አንድዬ አንተ ሁናት ብዬ ዝም እላለሁኝ። ለሞቱ ጊዜ ግን ትፈለጋለች። ወጣት ናሆሰናይ የተገበረው በዚህ ካልኩሌሽን ነበር። የጎንደር መናጥ ታልሞ። ማን አተረፈ??? ምን ተረፈ???   በመጨረሻው የጎንደር ጥምቀት በአንድ ቀን 28 ጊዜ በረራ እንደ ነበር አድምጫለሁ። በአውቶብስ የመጓዝ አጋጣሚው ቢኖርም ያኑ ያህል ይሆን ነበር። ግን ዋስትና የለም በአውቶብስ መጓዝ። ፈልጌ እማዳምጠው የተጋሩ ተዋህዶወችን ነበር። አዳኞች