ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 16, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ብቃት እንደ ወንዝ አሽዋ ከሜዳ አይታፈስ። ከሥልጠናም መሰጠትን ይጠይቃል።

ምስል
  ብቃት እንደ ወንዝ አሽዋ ከሜዳ አይታፈስ። ከሥልጠናም መሰጠትን ይጠይቃል።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       ዶር ለገሰ ቱሉ በተማሩበት ሙያ ለደረጃቸው በብቃታቸው ልክ ቢመደቡ ጥሩ ነው። የግድ እንደ ጋዜጠኛ፤ እንደ ሞጋች ማድመጥ ያለብኝን ጉዳይ #ችዬ ማድመጥ ግድ ይላል። የኮሜንኬሽን አገልግሎት ሙያ ብቻ ሳይሆን #መሰጠትን ይጠይቃል። አቅም፦ ችሎታ በሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ የሚመጣ ነው። አንባሳደር ፍጹም አረጋ ቀዳሚው ነበሩ። የጨመቱም - ብቁም ነበሩ።    ያው ቦታው ለኦሮሞ ሊቃናት #የተመደበ ነው። ከዬትኛውም ክልል ይወከል፦ ለዚህ የአብይዝም ሥርዓት የኦሮሞ ልጅነት መስፈርት ሆኖ ለስድስት ተከታታይ ዓመታት ቀጥሏል። እሺ ይሁንላችሁ ብንል፦ ግን ቢያንስ የሚደመጥ #ለዛ ያለው ሰብዕና፤ ለኢትዮጵያም የአቅም ልክ የሚደመጥ ሰው - ይመደብ። ትዕዛዝ አይደለም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የግል ዕይታ ነው። የአቶ ለገሰ ቱሉ አንደበትም፤ የንግግር ጥበብ አቅምም ውሱን ነው። በቀላል አገላለጽ ለኢትዮጵያ ተፈጥሮ #ሸክም ነው። አብዝቶ በውስጡ የታጨቀ ቂም እና በቀል፤ #ጥላቻ እና #ማንአህሎኝነት የተከዘነበት ነው። ይህ ደግሞ ተፈጥሯዊ ለሆነችው ለልዕልት ኢትዮጵያ #የገጀሞ ያህል ነው።   አንድአንድ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሊቃናት ጠሚር አብይን አላዳምጣቸውም ሲሉ አደምጣለሁ። እርግጥ ነው 365 ቀን ሙሉ የሳቸው ዲስኩር አለ። አንደበቶቻቸው ሚዲዮቻቸው፤ የጸጥታ አካሉ በሙሉ በአንድ መንፈስ ይናገራሉ። ሁሉን ለማዳመጥ የበዛ ታጋሽነትን እንደሚጠይቅ አውቂለሁኝ። ለታማሚው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተስፋ ግን ማድመጥ የግድ ነው። ካልተደመጠ በያትኛው አመክንዮ የትግል ታክቲክ እና ስትራቴጅ ሊነደፍ ይችላል? ...

#ብልህነት በጠራራ ጠሐይ #ሲያመልጥ - መልካም ዕድል ምልጥ። የBBC መረጃ ሊንክና ጭብጡን አያይዣለሁ፤ በቅድሚያ የእኔ ዕይታ።

ምስል
  • #ብልህነት በጠራራ ጠሐይ #ሲያመልጥ - መልካም ዕድል ምልጥ።   የBBC መረጃ ሊንክና ጭብጡን አያይዣለሁ፤ በቅድሚያ የእኔ ዕይታ።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       የቀደሙት የአበው እና የእመው ዊዝደም ጥንቃቄ እና ብልህነት እርቀቱ የትዬሌሌ ነው። የተከበሩ ወሮ ሳህለወርቅ ዘውዴን የፕሬዚዳንትነት ቦታ ለማስለቀቅ ጥድፊያ ነበር በአብይዝም ፖለቲካ። ከዛ በፊት ቦታውን ፈቅደው ይመኙት የነበሩት ነፍሳቸውን ይማረው እና ፕሮፌሰር ጴጥሮስ በዬነ በሥጋ መለዬትም #ጥድፊያ ነበር። በምን? እንዴት? ለምን?--------ሁሉም ያልገባኝ ሊገባኝም ያልፈቀድኩ ነበር በወቅቱ። ምን ታቅዶ/ ምን ሊከወን እንደሚችል #በአሳቻው ሎሬት ጠሚር አብይ አህመድ አሊ በጨረፍታ ነጠብጣቦችን አያይዤ ዕውነት ፍለጋ ብማስንም፦ አሁን ያለውን የአፍሪካን የመሪነት ደረጃ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ለመድረስ አልቻልኩም ነበር። ኢትዮጵያ በአራቱም ማዕዘን በተወጠረችበት በዚህ ዘመን እንደ መሪ ኢትዮጵያን በአፍሪካ #ቁልፍ ፖለቲካ ባላ እና ወጋግራ ሊሆንላት የሚችል ሁነቶችን አደራጅቶ መምራት የግድ አስፈላጊ ነበር። ጠሚር አብይ አህመድ የማያውኩት፤ የማይነካኩት አመክንዮ የለም።    ለዚህም ነው በቀጠናው ትርምስ በዚህም በዚያም ኢትዮጵያ ሆኖ በማያውቅ ሁኔታ ወቀሳ የምታዳምጠው። በተለይ አሁን በግሎባላይዜሽኑም #ትራንፒዝም ተገማች ክስተት አይደለም። ይህን አስታግሶ በልኩ፤ ለልኩ ለመምራት የአፍሪካ ቁልፍ የመሪነት ቦታ ኢትዮጵያ በእጅጉ ያስፈልጋት ነበር። ጥበቡ በዊዝደም ቢልቅ ቢቀልም ኖሮ።    ኢትዮጵያ #ተፈሪ ተከባሪም አገር ናት። ተፈሪነቷ፦ ቀደምትነቷ በታሪክ መመዝገቡ ብቻ ሳይሆን ዛሬ -- ዛሬ በዘመነ...