ልጥፎች

ከጁን 23, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ነገረ ኢህአፓ። ዕድሜ እኮ የኔታ ነው ውስጡን ለፈቀደ።

ምስል
  ነገረ - ኢህአፓ። ዕድሜ እኮ የኔታ ነው ውስጡን ለፈቀደ።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።" እንዴት አደራችሁ ማህበረ ቅንነት?   #ጠብታ ።   የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ላም እረኛ ምን አለን ዕውቅና ሰጥተውት እንደማያውቁ አውቃለሁኝ። ግን ውስጤን መግለጽ አይቋረጥም። ይቀጥላልም።    ኢህአፓን በሚመለከት ሚዲያ ላይ ተቀጥሬ እሰራ በነበረበት ጊዜ በስብሰባው ተገኜቼ ያየሁትን፤ የሰማሁትን ከመዘገብ ውጪ ኢህአፓን እንደ አንጋፋ የፖለቲካ ድርጅትነቱ ሞግቼው አላውቅም። ምክንያቴ እንደ ልፋቱ ዕድል ያልቀናው ባተሌ መሆኑን አውቃለሁኝ። ለአውራ የፖለቲካ መሪነት እንኳን ያልበቃ ነው ኢህአፓ። መንግሥት ሆኖም ስለአላየሁት ዕድል ለተላለፈው የፖለቲካ ድርጅት ምን ፍጠር ብየ ልሞገትው? ልተቸው። ኢህአፓ በመገበር የኖረ የፖለቲካ ድርጅት ነው።   እኔ የኢህአፓ #አባልም ፤ #አካልም ሆኜ አላውቅም። መንፈሱም አልተጠጋም ከእኔ። ምክንያቱም ጠንካራ እናት ስለነበረችኝ ማንኛውም እንቅስቃሴየን ትቆጣጠረው ስለነበር ወደ ኢህአፓ ትውር አላልኩም። "ትምህርት ቤት አትሂዱ፤ አትማሩ" የወቅቱ የኢህአፓ ሞቶ ነበር። እናቴ ግን ጥጧን የሚሳሳውን ይዛ፤ ደብተሬን በዘንቢል ተሸክማ ገብያ የምንሄድ መስለን ትምህርት ቤት እራሷ ትወስደኝ ነበር።   ትምህርቱ እስኪያልቅ ድረስ ጠብቃ በሄድንበት መንገድ ሳይሆን መንገድ #ቀይራ ወደ ቤት ትመልሰኛለች። ብዙ ማስጠንቀቂያወች በደጃፋ ሥር ከኢህአፓ ይላክም ነበር። የእናት፤ የፆታ፤ የሥርዓት ጭቆና አለባት ይሉ ነበር ኢህአፓወች። የማልሸሽገው ትምህርት ቤት ውስጥ፤ ከውጭም፤ በረፍት ጊዜም #ጭንቀቱ ከባድ ነበር። ስጋቱ አይጣልባችሁ። በዛ ላይ አባባ ጫካ ነበሩ። ...

#ያላለቀ #ዕዳ። #ያልተቋጬ #የትውልድ #የቤት #ሥራ።

ምስል
    #ያላለቀ #ዕዳ ። #ያልተቋጬ #የትውልድ #የቤት #ሥራ ።   "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ፤ እንደ ምህረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ።"   (መዝሙር ፶ ቁጥር ፩)   መቅድም።   የአቶ ታየ ደንዳንዳን መታየት አስመልክቶ እንደ ማንኛውም አድማጭ እንጂ እንደ አልፍኩበት የሚዲያም፣ የፖለቲካም ሕይወቴ አቋም ላይ ሆኜ አልተከታተልኩትም። መጀመሪያ አዲስ ኮንፓስ ከሌላ ሚዲያ አዘጋጅ ጋር የነበረውን ቆይታ አዳመጥኩኝ። በአቶ ታየ የፖለቲካ አቋም መጨከን የተሳነው ሆኖ ነው ያገኜሁት። ሌላ ገፊ ኃይል እንዳለው ያመነ ይመስላል የውይይቱ አጠቃላይ መንፈስ።   ሁለተኛ ያዳመጥኩት አንከር ሚዲያ ነው። "በድምጽ ለማስቀረት" የሚለውን ስሰማ ደንግጫለሁኝ። በሌላ በኩል የውይይቱ አየር የሹክሹክታ ሁነት መኖሩም ሌላ ክስተት ነበር። በተጨማሪም የጋዜጠኛ መሳይ መኮነን የመሻት አቅጣጫን ለመመዘን ጊዜ ሰጥቸ ተከታትየዋለሁኝ። የመሻት ጭነቱን መጠን እንደማለት።   ከዛ ቀጥየ ክፍል ፩ እና ፪ አንከር ሚዲያ በአቶ ታየ ደንድዓ የፖለቲካ አቋም ከረ/ ፕሮፌሰር ትንግርቱ ጋር ያደረገውንም ቆይታ ታደምኩኝ። ከዚህ በኋላ ነበር ከመሠረቱ ሚዲያ ሆርን ኮንቨርሴሽን ሦስቱንም ክፍል ማስታወሻ እያያዝኩ ያዳመጥኩት።    በውነቱ አወያዩ በተረጋጋ መንፈስ ካልተበራከተ መጫን ጋር በእርጋታ ቀለል ባለ የአጠያዬቅ ዘይቤ የአቶ ታየ ደንዳን የውስጥነት የመግለጥ አቋም ጊዜ ሳይሻማ፤ እንዲሁም ወደ ሌላ አቅጣጫ እንዲያማትር ሳያደርግ በፍጹም ጨዋነት የተካሄደ ነበር። ያልገባኝ ግን አወያዩ የኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር ሳይሆን የሚለው "የጎርጎሪያውያን፣ የግዕዝ አቆጣጠር" እያለ ነበር ድርጊቶች የተከወኑበትን ቀናት፣ ወራት እና...