ልጥፎች

ከኦክቶበር 15, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ጠ/ ሚር ዶር አብይ ለልዩ ሃይሉ ትህትና መቀለባቸውን እደግፈዋለሁ።

ምስል
መጋጋል ። „እግዚአብሄር የእውነት ዳኛ ነው፤ ሃይለኛም ታጋሽም ነው። ሁልጊዜ አይቆጣም“ ከሥርጉተ© ሥላሴ  13.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። በሰሞናቱ የልዩ ሃይል አመጥ ጉዳይ የሁለገብ ሊቀ ሊቃውነቱ ሻለቃ ዳዊት የሰጡትን ቃለ ምልልስ አዳመጥኩት። ያው ሙያዊ ነው። እሳቸው ሉላዊ ዕውቀትም፤ ልዩ ተመክሮም ያላቸው ሊሂቅ እጬጌም ናቸው። በሌላ በኩል መጀመሪያ ላይ ከምንም ያልቆጠሩት ሁሉ አሁን ውይይቱ ሦስት ቀን ነበር ሲባል ማጋጋሉን ተያይዘውታል። መጀመሪያ ላይ ነው ጠረኑ ትክክል አለመሆኑን በርቀት ማዬት፤ ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ ለመንግስት መስጠት። ቀደም ብሎ ጉዳዩን ማጥናት፤ መተንተን እና መረጃውን ከተለያዬ አቅጣጫ የመገምገም ምህንድስና ሊደረግበት ነበር የሚጋባው። ቀድሞ ነገር እንደዚህ ያለ ነገር ሲደመጥም ወዲያው ማብራሪያ መስጠትም የተገባ አይደለም። ችኮላ አያስፈልገውም። ተደሞ ያስፈልገዋል። ርጋታ እና ስክነትም ይጠይቃል። አሳድሮ አገላብጦ አይቶ ከስሜት ጋር ሳይስጠጉ፤ በራስ ፍላጎት ሳይቸነክሩ የጭብጡን ማንነት ብቻ በራሱ ማንነት ራሱን አስችሎ መመርመር ነበር የሚገባው። የሆነ ሆኖ እኔ አስተያዬቴን ዛሬ ልሰጥ የፈልግኩበት ምክንያት ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮወርጊስ ዕይታ ጠ/ ሚር አብይ አህመድ የወሰዱት እርምጃ ትክክል አይደለም የሚሉትን ነው። እሳቸው ዘመን ጠገብ ባለሙያ ስለሆኑ እሳቸውን አሻቅቤ መተቸት አልችልም። ክህሎቱም ተመክሮውም ብልጹግ ነው በሲቢሉም ሆነ በወታደራዊ። መሬት ላይም ሰርተውበታል። ነገር ግን እኔ እንደ ሰው ጠ/ ሚር አብይ አህመድ የወሰዱት እርምጃ ትክክል ነው ብዬ ነው እማስበው ። ጠ/ ሚር አብይ አህመድ እያስተማሩ ያሉት የሃሳብ አቅም ከባዱን ተራራ ንዶ፤ ደልድሎ፤ ሸካራውን ለግ

ግልጽነት ገዳም በመግባቱ ቋቅ ነገሰ።

ምስል
ግልጽነት ገዳም በመግባቱ ቋቅ ነገሠ። "እናንተ የሰው ልጆች እስከ መቼ ድረስ       ልባችሁን ታክብዳላችሁ?" ሐሰትንም ለምን ትሻላችሁ?"  መዝሙር ፬ ምዕራፍ ፪  ከሥርጉተ © ሥላሴ  15.10.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። እኔ የሚገርመኝ ብሄራዊ የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ የያዙት በአደባባይ ተረሽነው 1200 ነፍሶች ጦላይ ላይ ባለቤት፤ ጠያቂ ሁነኛ ድርጅት ሳይኖራቸው ፍዳቸውን እያዩ በሌላ በኩል ደግሞ የብሄራዊ ሰንደቅዓላማ ቀን ሰሞን ምክክር ውይይት ዲስኩር ይደመጣል። ይህን አጣጥሙ መጀመሪያ። እኔ አይደለም የምላችሁ ፋክት ነው የሚያፋጥጠው የጠ/ ሚር ጽ/ቤትን። እኔ እኮ የማይጠቅመው ነገር እንደሚጠቅም ሁሉ እንዲቀጥል የሚፈቀደልት ምክንያት ነው የማይገባኝ። ትናንት የኤርትራው ፕሬዘዳንት አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ኢትዮጵያ ጎራ እንዳሉ አዳመጥን። ያዳመጥነውን አላምጠን መወጥ ይገባ ስለነበር እኔ አቶ ዳውድ ኢብሳ የኢትዮጵያን መንግሥት እያስደገደጉ ነው ብዬ ነው እማስበው ብዬ የጻፍኩትም ለዚህ ነው። አቶ ፍጹም አረጋ ደግሞ ይህን አስተባብለዋል በዓለም አቀፍ ሚዲያ ወጥተው። ሆደ ሰፊነት ይሆን 5 ወጣቶችን በአደባባይ አስረሽኖ 1200 ባለቤት አልባዎችን ጦላይ ፍዳ እያስከፈለ፤ የጫት፤ የሺሻ፤ የቁማር፤ የዝርፊያ ፓርቲ ተፈጥሮ የተለጠፈላቸው፤ ጎንደር እና ወሎ ተነጥለው ከዛ የመጡ ወንጀሎኞች ማለትስ ምን ማለት ነው? አይገባንም ይህ? ልብም ህሊናም አለን። ግልጽነት አዲስ ለውጥ አራማጆች መርህ ይሆናል ተብሎ ታውጆ እምናዬው እምንስማው ግን ድብቅነት እንደ ነገሠ ነው። ከስሜን አሜሪካ ከጠ/ ሚር ጉዞ መልስ ጀምሮ ያሉ ነገሮች በህልማችን ለምናምን ሰዎች ዕድምታውን እናውቀዋለን። ወንበሩ ባ