ልጥፎች

ከሜይ 10, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ጎንደር ክፍል - አራት፤ ማጠቃለያ።

ምስል
                     ጎንደር ክፍል - አራት          የጎንደር መንፈስ               ይጠራል።                                 ከሥርጉተ ሥላሴ 05.06.2014 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)                    „የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው። በርሱ ለሚታሙኑ ሁሉ ጋሻ ነው።“                                           (መዝሙር ምዕራፍ ፲፯  ቁጥር ፴) „የበለጠና የከበደ ኃላፊነት እንደሚጠብቀኝ ባውቅም ለእኔ የከበደኝ ግን ከጎንደር ህዝብ መለዬቴ ነው“ ጓድ አበበ በዳዳ የጎንደር ክ/ ኢሠፓ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ ለጂንካ የክ/ ኢሠፓ አንደኛ ጸሐፊ ሆነው ሲሄዱ መሸኛቸው ላይ የተናገሩት ነበር። የጎንደር አቀራረብና የአያያዝ ሙያው ከውስጥና በመሆን ሰንደቅ የከበረ ነው። ጎንደር ኖሮ መለዬት ትዝታዎቹ በቀላሉ ሊፋቁ የማይችሉ፤ እንዲያውም ትውስታዎች እያመረባቸውና ወዘናቸው እዬፈካ በናፍቆት አሳምረው የሚያሹ፤ በራሳቸው ጊዜ በመንፈስ ቤተኛ መሆን የሚችሉ፤ ተመክሮን ያስመቹና ያሰበሉ የመልካምነት ማሳ ናቸው። የማከብራችሁና የምናፍቅቻሁ የሀገሬ ልጆች ጹሑፉ ተከታታይ ይሆን ዘንድ ክፍል ሦስት ማጠቃለያው እንዲህ ይል ነበር።  --- ሌላው ቀርቶ የታሪካችን አካል የሆነው የግራኝ መሐመድ እረፍት እኮ ጎንደር ነበር። ደንቢያ ላይ የግራኝ በር ይባላል። በነገራችን ላይ በዛ ዘመን የትግራዩ እንደርታና የጎንደሩ ደንቢያ በከንቲባ የሚተዳደሩ ዕውቅና የነበራቸው ከተሞች ነበሩ።  ዛሬ ግን የእንደርታን ባላውቅም፤ አይደለም ደንቢያ ጎንደር አንዲት መንደር ናት በጨለማው ዘመነ በወያኔ - የታሪክ ረግረግ። ታሪክ ማለት እንደ ሥርጉተ ዕይታ - የህዝብ ወላዊ አዎንታዊ

ጎንደር - ክፍል ሦስት።

ምስል
                                               ጎንደር - ክፍል ሦስት።                                                ከሥርጉተ ሥላሴ 29.05.2014 (ሲዊዘርላንድ ዙሪክ)                  „አረማመዴን በበታች አሰፋህ፣ እግሮቼም አልተንሸራተቱም።“ (መዝሙር ፲፯ ቁጥር ፴፮) „ለመደመጥ የጥሩ አድምጩን የጎንደርን ህዝብ ሥነ ልቦና በጥንቃቄ መርምሮ ማወቅ ይገባል፤ ጎንደር መሆን ነውና!“ ጓድ ገብረመድህን በርጋ የጎንደር ክፍለ ሀገር የኢሠፓ ዬድርጅት ጉዳይ ኃላፊ በነበሩበት ጊዜ በአጽህኖት - በተደጋጋሚ የሚቃኙት ቅኔ ነበር። ሲገፉም አብሮ ለመሰለፍ ያስቻለው፤ ቋሚ ጽናት የመነጨው ከዚህ ንጹሕ ፍቅርና እርግጠኝነት እንዲሁም የበቃ አቅማቸው የተፈለፈለ ነበር። እስከ መጨረሻዋ ቀን ድርስ አብረን ነበርን። ማናቸውንም መስዋዕትነት ከፍለን። ጓድ ገዛህኝ ወርቄና ጓድ ገ/መድህን በርጋ አብረው የመሥራት አጋጣሚ ኖሯቸው ቢሆን ኖሮ ህዝበ - ጠቀም  ትዕይንቱ ጎንደር ላይ እጬጌ በሆነ ነበር። ሁለቱም በቂና ሙሉ የመምራት አቅምና ብቃት፤ የህዝብ የጸዳ ንዑድ ፍቅር፤ ከቶውንም ሊገለጽ የማይችል የሥራ ፍቅር ጉልታቸው ነበርና። ለእኔ ህሊናዎቼ ናቸው - ዬምኮራባቸው። እጅግ የማከብራችሁ የሀገሬ ልጆች ባለፈው ጊዜ ክፍል ሁለትን በዚህ መልኩ ነበር የደመደምኩት። እንዲህ … ክፍል ሁለት ማጠቃለያው --- በዬዘመናቱ መበደሉን እያወቀ ግን በአርምሞና በትእግስት የላቀ ች ውን ዬእናት ሀገሩን ጉዳይ በማስቀደም በተደሞና በአርምሞ እንዲሁም በጭምትንት የተቀመጠን ህዝብ ሰብዕና፤ ከእኛም አልፎ ዬዐለም ሃብትና ቅርስ የሆኑ ውድ ጌጦቻችን ያበረከተ ንቁ ህዝብ፤ ለማንኛውም ቋያ ነክ ግዳጅ መቆስቆሻ

ጎንደር - ክፍል ሁለት ።

ምስል
     ጎንደር - ክፍል ሁለት ።                            ከሥርጉተ ሥላሴ  25.05.2014 (ሲወዘርላንድ ዙሪክ)                 „አቤቱ በአንተ ታምኛለሁ እና ጠብቀኝ።“  (መዝሙር ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፲፩)    ·        እፍታ። „መታደሌን የማውቀው ከጎንደር ጠንካራ፣ ቅንና እና ግልጽ ህዝብ ጋር እንድሠራ ፓርቲዬ ኢሠፓ ስለፈቀደልኝ ነው። ስለዚህም ከጎንደር የበቃ ታሪክና ታታሪ ህዝብ ጋር ሆኜ ማናቸውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነኝ። የጎንደር ክ/ሀገር ህዝብ እምነት የሚጣልበት፤ ኃላፊነት የሚሰማው ልዩ ኃይል ነው።“ ይህን  አፈሩ ይቅለላቸውና እኒያ ቅንና ብሩክ ጓድ ገዛህኝ ወርቄ የኢሠፓ ማዕከለዊ ኮሜቴ አባልና የጎንደር ክፍለሀገር ኢሠፓ አንደኛ ጸሐፊ በህይወት በነበሩበት ጊዜ በሙሉና በአጥጋቢ ኢትዮጵያዊነት ስሜት የተናገሩት ነበር። እንዳሉትም አደረጉ። በ18 ቀኑ የጎንደር የፋመ የመከላከል ውጊያ ኤሊኮፍተር ከማዕከላዊ መንግስት ቢመጣላቸውም የጎንደርን ህዝብንና ጓዶቼን ከእሳት ማግጄ እኔ አዲስ አበባ ብቻዬን አልሄድም ብለው ኮማንድ ፖስታቸውን ወደ ላይ አርማጭሆ አዙረው፣ ቀና ድጋፍ ከመንግሥት አገኝቼ ለድል እንበቃለን ሲሉ ጦርነቱ የእርስ-በእርስ ስለነበር፤ እንዲሁም ጎንደር ላይ የወያኔ ቅስም ቢሰበር ጸጉራቸው የሚቆሙት ሽውራር ስሜቶችም ታክለው የታሰበው ሳይሆን ቀረ። እሳቸውም በወሰዱት ጥንቃቄያዊ በሳል እርምጃ ጎንደር ከተማ አንዲት ነፍስ ሳይጠፋ፤ ቅርሶቿም በጠላት ሳይወድሙ ህይወታቸው እስከ ልጃቸው ድረስ ጎንደር - አርማጭ ሆ ላይ ቀረ።                                                     እጅግ የማከብራችሁ የሐገሬ ልጆች በውስጥ መኖርን ለመትርጎም ውስጥን

ጎንደር ክፍል አንድ።

ምስል
     ጎንደር ክፍል አንድ።                      ከሥርጉተ ሥላሴ 05.04.2014 ( ሲዊዘርላንድ -   ዙሪክ )    „እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች የሚያረታ በኮረብቶችም የሚያቆመኝ እግዚአብሄር ነው“                             መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፲፯ ቁጥር ፴፫ „ የጎንደር ከተማ ስትነሣ የፋሲል ግንብ፣ የፋሲል መዋኛ እና ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ናቸው በብዛተ የሚጠቀሱት። በከተማዋ ወስጥ ግን ከምድር በላይም ሆነ ከምድር ሥር ያልታወቁ እና የተዘነጉ አያሌ ቅርሶች ይገኛሉ። “ ( ከዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተጻፈ ከማህበረ ቅዱሳን ማህበራዊ ድህረ ገጽ የተወሰደ ) ·        ስሜት ያልተዳሰሰ ግዙፍ ተፈጥሮ። እንደ እኔ ስሜት ሆኖ ማሰብ ይከብዳል። በእኔ ስሜት ውስጥም ጫና ፈጥሮ ስሜቱን ለመሸጥም የሚችለው ለስሜቴ የሚመች ቅርብ ሲኖር ብቻ ነው። ስሜት ሁሉን ሰንቆ ይራመዳል። ስሜት ድምጽ አልባ ቋንቋ ነው። ቋንቋውም ጠንካራና ደንበር አልባ ነው። የውስጥ ስሜት ቋንቋው አካባቢያዊ ተፈጥሮን ንዶ፤ ተርጓሚ ባለሙያን ሥራ አጥ የሚያደርግ ረቂቅ ግን ጉልበታም፤ የማይታይ ውጤቱ ግን የሚዳሰስ … የሚጨበጥ ሚስጥራዊ ተፈጥሮ ያለው ነው። በዚህ መንፈስ አብረን እንጓዝ ዘንድ ለመንኩ ጸሐፊዋ ሥርጉተ ሥላሴ። ለእያንዳንዱ ሰው የተፈጠረለትን የማንነት ዲካ በቅጡ በመፈተሽ እንደ እራስ ለመኖር በማስተዋል ተፈጥሯዊ መክሊትን ልብ ብሎ ማድመጥ ይገባል። በመሃል ሽርፍራፊ ነገሮች አውዱን እንዳያወከውም ጠራርጎ ማስወጣት ይገባ